ከዚሁ አንፃር ኩባንያችን ህብረተሰቡ ስለ ቫይረሱ ግንዛቤ እንዲኖረው እና ያለመዘናጋት እራሱን ከቫይረሱ አንዲጠብቅ ሰፊና ተደራሽ የሆኑ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎችን በተከታታይ በመሥራት ላይ የሚገኝ ሲሆን ለአብነት ያህልም በመላው አገሪቱ የሚገኙ  የሞባይል አገልግሎት ደንበኞች ጥሪ በሚደርጉበት ጊዜ ጥሪያቸው ከመነሳቱ በፊት የተቀረፀ የድምፅ መልዕክት እንዲያደምጡ በማድረግ፤ በ444 አጭር ቁጥር እንዲሁም በቀን ከአራት መቶ ሺህ በላይ ደንበኞች በሚስተናገዱበት 994 ነፃ የጥሪ ማዕከል አማካኝነት በአማርኛ፣ በኦሮምኛ ፣ በሶማልኛ ፣ በትግሪኛ እና በአፋርኛ ቋንቋዎች የተቀረፁ የድምፅ መልዕክቶችን በማስደመጥ፤ ለሞባይል ደንበኞች የድምፅ እና የፅሁፍ መልዕክቶችን በመላክ፤ አንዲሁም በማህበራዊ ትስስር ገፆች እና ሰፊ ተመልካች ባላቸው የተቋሙ የአደባባይ እስክሪኖች ስለቫይረሱ ጠቃሚ መረጃ በመስጠት ላይ ይገኛል፡፡

Share This Post:

Share on facebook
Share on telegram
Share on twitter
Share on linkedin

Follow Us

Recent Posts

Archives