ኢትዮ ቴሌኮም ያገለገሉ የተለያየ ሞዴል ያላቸውን ተሽከርካሪዎች ባሉበት ሁኔታ በዝግ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡

  1. ዝርዝር መረጃ የያዘውን የጨረታ መወዳደሪያ ሰነድ ተጫራቾች ከጥቅምት 01 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ጥቅምት 30 ቀን 2014 ዓ.ም ከሰኞ እስከ ዓርብ ዘወትር በስራ ሰዓት የማይመለስ 100.00 (ብር አንድ መቶ) በመክፈል ከአቃቂ ዕቃ ግምጃ ቤት መግዛት ይችላሉ፡፡
  2. ተሽከርካሪዎቹን ለማየት ለሚፈልጉ ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የገዙበትን ደረሰኝና መታወቂያ በመያዝ አቃቂ በሚገኘው ኢትዮ ቴሌኮም ዕቃ ግምጃ ቤት  በመገኘት  ከጥቅምት 01 ቀን 2014 ዓ.ም እስከ ጥቅምት 30 ከጠዋት 5፡30 ብቻ በዓላትን ሳይጨምር ማየት ይችላሉ፡፡
  3. ተጫራቾች በጨረታዉ ለመሳተፍ የጨረታ ውጤት ከታወቀ በኋላ የሚመለስ የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ለአንድ መኪና 20 ሺህ ብር ከአንድ መኪና ባላይ የሚጫረቱ ከሆነ ለእያንዳንዱ 20 ሺህ ብር አስልተው ከታወቀ ባንክ ተረጋግጦ በሚቀርብ ሲፒኦ (CPO) በማሰራት ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
  4. ተጫራቾች ለመግዛት የሚፈልጉትን ተሸከርካሪ የሚገዙበትን ዋጋ በጨረታ ሰነዱ ላይ በሚቀመጠዉ ዋጋ ማቅረቢያ ቅጽ/ ፎርም መሰረት ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
  5. ጨረታዉ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸዉ በተገኙበት አቃቂ በሚገኘው ኢትዮ ቴሌኮም ዕቃ ግ/ቤት ኅደር 01 ቀን 2014 ዓ.ም ከጠዋቱ 5፡00 ሰዓት ይከፈታል፡፡

                                    ኢትዮ ቴሌኮም

 

Share This Post:

Share on facebook
Share on telegram
Share on twitter
Share on linkedin

Follow Us

Recent Posts

Archives