መላ (አነስተኛ ብድር)

ይህ የአገልግሎት አይነት ለግለሰብ እና ለነጋዴዎች/ወኪሎች አነስተኛ ንግድ/ቢዝነስ እንዲጀምሩ ወይም እንዲያስፋፉ በኤሌክትሮኒክ ገንዘብ አነስተኛ መጠን ያለው ክሬዲት የሚያገኙበት የአገልግሎት አይነት ነው።

መላ ሳምንታዊ እና ወርሃዊ

የብድር ዓይነት

የብድር ዓይነትትንሹ የብድር መጠንትልቁ የብድር መጠንየመክፈያ ጊዜየአገልግለት ክፍያየቀን ክፊያቅጣት
መላ ዕለታዊ1002,0001 ቀን1% 2%
መላ ሳምንታዊ1005,0007 ቀናት1%0.35% እስከ 1.2%2%
ማስታወሻ: ሁሉም የገንዘብ መጠኖች በብር የተቀመጡ ናቸው፡፡

ወርኃዊ መላ

የክሬዲት መጠንታሪፍ
የአገልግሎት ክፍያዕለታዊ ክፍያቅጣት
6003%0.80%0.11%
800 0.75%
1,400 0.70%
3,000 0.67%
6,000 0.62%
8,000 0.58%
10,000 0.50%
12,000 0.30%
ማስታወሻ: ሁሉም የገንዘብ መጠኖች በብር የተቀመጡ ናቸው፡፡

የ50 ቀናት መላ

የክሬዲት መጠንታሪፍ
የአገልግሎት ክፍያዕለታዊ ክፍያቅጣት
30006%0.70%0.11%
5,000 0.66%
7,000 0.62%
9,000 0.59%
11,000 0.56%
13,000 0.53%
15,000 0.50%
18,000 0.50%
ማስታወሻ: ሁሉም የገንዘብ መጠኖች በብር የተቀመጡ ናቸው፡፡
የብድር   ;አይነት ትንሹ የብድር መጠን ትልቁ የብድር መጠን የመክፈያ ጊዜ የአገልግሎት ክፍያ ቅጣት
መላ እለታዊ 100 2,000 1   day 1% 2%
መላ ሳምንታዊ 5,000 7   Days 1% 0.50%
መላ ወርሃዊ 10,000 1   Month 3%

ለመላ ክሬዲት ተለዋዋጭ ዋጋ

 ሳምንታዊ
ወርሃዊ
የብድር መጠን አገልግሎቱን ለማግኘት የሚከፈል እለታዊ ክፍያ እለታዊ የቅጣት ክፍያ
የብድር መጠን አገልግሎቱን ለማግኘት የሚከፈል እለታዊ ክፍያ እለታዊ የቅጣት ክፍያ
ትንሹ የመጨረሻው
ትንሹ የመጨረሻው
100 5000 1% 0.35% 0.50%
100 10000 3% 0.35% 0.50%
4000 0.40%
8000 0.40%
3000 0.85%
6000 0.65%
2000 1.05%
2500 0.85%
1000 1.10%
1000 1.05%
100 1.20%
200 1.20%

መዳረሻ

መዳረሻ የቴሌብር መላ አገልግሎት አንዱ አካል ሲሆን በቴሌብር ደሞዛቸውን ለሚቀበሉ የመንግስት እና የግል ሰራተኞች ክሬዲት እንዲያገኙ የሚያስችል አገልግሎት ነው፡፡

                          መላ መዳረሻ

ምርት

ዝቅተኛ

ከፍተኛ

የአገልግሎት ክፍያ

የክሬዲት መጠን

1000

36000

 

የመመለሻ ቀነ ገደብ

90 ቀናት ወይም 3 ወር

 

 

የብድር መክፈያ ጊዜ

በየወሩ

 

 

ከመመለሻ ቀነ ገደብ ወይም 90 ቀናት በኋላ

 

0.5%  በቀን

 

ማስታወሻ፡

  • የብድር ገደብ ከብር 1,000 እስከ 36,000 ነው።
  • የመመለሻ ቀነ ገደብ ከ90 ቀናት በኋላ ይሆናል….

መላ መዳረሻቴሌብር መተግበሪያ አገልግሎት ለመጠቀም

  1. የፋይናንስ አገልግሎትን ይምረጡ
  2. ቴሌብር መላን ይምረጡ
  3. መላ መዳረሻን ይምረጡ
  4. ክሬዲት ገደብዎን ይመልከቱ
  5. ክሬዲት ይጠይቁ የሚለውን
  6. የብር መጠን አስገብተው ይመልከቱ የሚለውን ይጫኑ
  7. ለመጨረስ ያረጋግጡ የሚለውን ይጫኑ

በአጭር ቁጥር *127# በመደወል

  1. *127# ይደውሉ
  2. ለፋይናንሽያል አገልግሎት 1ን ያስገቡ
  3. ለቴሌብር መላ 1ን ያስገቡ
  4. ክሬዲት ለመውሰድ 1ን ይምረጡ
  5. ወደ ቀጣይ ማውጫ ለመሄድ (#) ን ቀጥሎ መዳረሻ 3 ወርን ለመምረጥ 4ን ያስገቡ
  6. በቀጣይ ማውጫ (#) የሚፈልጉትን የክሬዲት መጠን ያስገቡ
  7. ለማረጋገጥ 1ን ያስገቡ

  • የመዳረሻ ክሬዲት አገልግሎትን ለማግኘት ሰራተኞች በቅድሚያ የውል ስምምነት መፈጸም ይገባቸዋል፡፡
  • ሰራተኞች በ90 ቀናት ውስጥ ብድሩን ከመለሱ የአገልግሎት ክፍያው 10% ይሆናል።
  • ከብድር መክፈያ ቀነ ገደቡ በኋላ ተበዳሪዎች በቀን5% ከጠቅላላው ቀሪ ክፍያ እንዲከፍሉ ይደረጋል።
  • ደመወዛቸው በቴሌብር ገቢ ሲደረግ የተመላሽ ክፍያው ወዲያውኑ ተቀናሽ/ተፈጻሚ ይሆናል።
  • ሰራተኞች የደሞዛቸውን 30% መበደር ይችላሉ።
  • ከፋይ/ቀጣሪ ድርጅቱ እና እና ሰራተኞች ደሞዛቸውን በቴሌብር ለመቀበል የሚያስችል ስምምት ማድረግ ይገባቸዋል፡፡
  • የመዳረሻ ብድር አገልግሎትን ለማግኘት ሰራተኞች 3 ጊዜ (ወራት) ደሞዛቸውን በቴሌብር መቀበል ይጠበቅባቸዋል።
  • የኮንትራት ውሉ ሲፈረም የደመወዛቸውን 30% በክሬዲት እንዲወስዱ የሚያስችል ይሆናል።
  • ክሬዲቱ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ የሚከፈል ይሆናል፡፡
  • ቀጣሪ ድርጅቱ/ኩባንያው የሰራተኞቹ የደሞዝ ክፍያ በቴሌብር መክፈሉን እንደሚቀጥል በማረጋገጥ እንንሁም ኮንትራቱን ሲያቋርጥ ከአንድ ወር በፊት ለኢትዮ ቴሌኮም ማሳወቅ አለበት።

የቴሌብር መላ አገልግሎት ለማግኘት ብቁ የሚያደርጉ መስፈርቶች

  • የደንበኛ የመበደር አቅም ደንበኛው ባደረገው የ6 ወር የቴሌብር የገንዘብ እንቅስቃሴ እና በቴሌኮም አጠቃቀም ይወሰናል።
  • በተጨማሪም ከታች ያሉት የቴሌብር ግብይቶች እና የገንዘብ ልውውጥ የደንበኛ የብድር አቅምን ለማስላት የሚውሉ ይሆናል።
    • ለእርስዎ ወይም በስጦታ የአየር ሰዓት መሙላት ወይም ጥቅል
      መግዛት (በራስ አገዝ ወይም ከወኪሎች)
    • ዕቃ ወይም አገልግሎት ግዢን መፈጸም
    • ለእርስዎ ወይም የሌላ ደንበኛ ቢል ክፍያ (በራስ አገዝ ወይም
      ከወኪሎች) ማከናወን
    • ለእርስዎ ወይም የሌላ ደንበኛን የፍጆታ አገልግሎት ክፍያ (በራስ አገዝ ወይም ከወኪሎች) መፈፀም
    • ከውጭ አገር ገንዘብ መቀበል
    • የጅምላ ክፍያ (ደሞዝ፣ ሴፍቲኔት…) መፈፀም 
    • የትኬት ክፍያ መፈፀም
    • ለገንዘብ ማሰባሰቢያ የእርዳታ ክፍያ መፈፀም
    • የቁጠባ አገልግሎት
    • የቴሌኮም ፍጆታ (ድምጽ፣ ዳታ ወይም መልዕክት) መፈፀም

• ከቴሌኮም አገልግሎት ፍጆታ በተጨማሪ ቢያንስ አንድ የቴሌብር አገልግሎት መጠቀም ይኖርብዎታል፡፡
• የ6 ወራት ግብይት ወይም አጠቃቀም ለብቁነት መስፈርት የሚቆጠር ይሆናል።
• በሚፈቀደው ዝቅተኛ እና ከፍተኛ የክሬዲት መጠን መካከል ማንኛውንም መጠን መበደር ይችላሉ።

የቴሌብር መላ አገልግሎት ለማግኘት ብቁ የሚያደርጉ መስፈርቶች

  • 18 አመት እና ከዚያ በላይ
  • አገልግሎት የሚሰጥ የኢትዮ ቴሌኮም ሲም ካርድ መያዝ
  • የቴሌብር እና የኢትዮ ቴሌኮም አገልግሎቶችን እንደ ዳታ/ድምጽ/አጭር የጽሁፍ መልዕክት መጠቀም ይኖርብዎታል፡፡
  • ለመመዝገብ በአጭር ቁጥር (*127#) ወይም በቴሌብር መተግበሪያን ይጠቀሙ፡፡
  • የቴሌብር የደንበኝነት ቆይታ 3 ወር እና ከዛ በላይ መሆን ይኖርበታል፡፡

በቴሌብር
የሞባይል መተግበሪያ
እንዴት አገልግሎቱን ማስጀመር እና መጠቀም እችላለሁ?

አገልግሎቱን ለማስጀመር

  • የፋይናንስ አገልግሎት የሚለውን ይጫኑ
  • ቴሌብር መላ የሚለውን ይምረጡ _ ደንብ እና ሁኔታዎችን በማንበብ የ √ ምልክት በመጫን መስማማትዎን ይግለጹ
  • ለማስጀመር የሚለውን ይጫኑ

ክሬዲት ለመውሰድ

  • ቴሌብር መላ ከሚለው ስር የሚፈልጉትን ኮንትራት ይምረጡ
  • የክሬዲት ገደብዎን እና የክሬዲቱን ዝርዝር ደንቦች ይመልከቱ
  • ክሬዲት ይጠይቁ የሚለውን ይምረጡ
  • የክሬዲት መጠን ያስገቡ
  • ይመልከቱ የሚለውን ይጫኑ
  • ያረጋግጡ የሚለውን በመጫን ይጨርሱ

ክሬዲት ለመክፈል

  • ቴሌብር መላ ከሚለው ስር የእኔ ቴሌብር መላ የሚለውን ይምረጡ
  • የሚከፍሉትን ኮንትራት ይምረጡ
  • በውል ዝርዝር ስር ይክፈሉ የሚለውን ይጫኑ
  • የሚከፍሉትን የብር መጠን ያስገቡ (በሙሉ ወይም በከፊል)
  • ያረጋግጡ የሚለውን በመጫን ይጨርሱ

ለግለሰብ ደንበኞች

  • 18 ዓመት እና ከዚያ በላይ ዕድሜ፣
  • ደንበኛው በስድስት ወራት ውስጥ ያከናወናቸው ግብይቶች ማለትም
    • የአየር ሰዓት እና ጥቅል መግዛት፣
    • የኢትዮ ቴሌኮም አገልግሎቶች (ድምጽ፣ አጭር ጽሁፍ እና ዳታ) አጠቃቀም፣
    • የኢትዮ ቴሌኮም ኔትዎርክ የቆይታ ጊዜ፣
    • ምርቶችንና አገልግሎትን መግዛት፣ ወርሃዊ የአገልግሎት ክፍያዎችን መፈጸም፣
    • የገቢ ማሰባሰቢያ ክፍያ፣
    • ገንዘብ ለመላክ፣
    • ገንዘብ ተቀማጭ ማድረግ፣
    • ገንዘብ ወጪ ማድረግ፣
    • ከውጭ ሃገር ገንዘብ መቀበል፣
    • በአንዴ ብዙ ክፍያዎን መፈጸም (ደመወዝ፣ ሴፍቲኔት..)፣
    • ትኬት መግዛት፣
    • ከዚህ በፊት የነበር የብድር ታሪክ፣ ወዘተ ግምት ውስጥ የሚገቡ ይሆናል፡፡
  • ደንበኛው ከዚህ በፊት የወሰደውን አነስተኛ ብድር ካልመለስ መበደር አይችልም፡፡
  • የአነስተኛ ብድር፣ የአየር ሰዓት ብድር እና የኢትዮ ቴል አገልግሎት ብድር ያለበት ደንበኛ ለአስተኛ ብድር አገልግሎት ብቁ አይሆንም፡፡

ለነጋዴዎች ወይም ወኪሎች

ሀ. ወኪል

    • ወኪሉ ለብድር አገልግሎቱ ተጨማሪ የውል ስምምነት መፈጸም ይኖርበታል፣
    • ወኪሉ ባለፉት ሶስት ወራት ውስጥ በቴሌብር ጥሩ የስራ እንቅስቃሴ ያለው፣
    • በተጨማሪም የጥቅል ሽያጭ፣ ወርሃዊ የአገልግሎት ክፍያ መፈጸም፣ ገንዘብ ወጪ ማድረግ፣ የአየር ሰዓት መሙላት፣ ለቴሌብር አገልግሎት የተመዘገቡ ደንበኞች ብዛት እና የደንበኝነት ደረጃ ማሳደግ፣ የብድር መመለስ ሁኔታ ግምት ውስጥ የሚገቡ ይሆናል፡፡

ለ. ነጋዴ

    • ለብድር አገልግሎቱ ተጨማሪ የውል ስምምነት መፈጸም እንዲሁም የታደሰ ንግድ ፍቃድ እና የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ማቅረብ።
    • ነጋዴው ባለፉት ሶስት ወራት ውስጥ በቴሌብር ጥሩ የስራ እንቅስቃሴ ያለው እንዲሁም በቴሌብር ክፍያዎችን የተቀበለ፣ በቴሌብር ምርትና አገልግሎቶችን የሸጠ፣ የአየር ሰዓት የሞላ መሆን ይገባዋል፡፡
    • በተጨማሪም የወሰዱትን ብድር በቶሎ መመለስ በድጋሚ ለመበደር ያስችላል፡፡
    1.  

ይህ ዉል (ከዚህ በኋላ "ደንቦች እና ሁኔታዎች" እየተባለ የሚጠራው) የቴሌብር መላ የብድር አገልግሎት ላይ ተፈጻሚ የሚሆኑ አጠቃላይ ደንብ እና ሁኔታዎች ያካትታል፡፡
እነዚህ ደንቦችና ሁኔታዎች እንዲሁም ከዚህ ጋር የተያያዙ ማሻሻያዎች እና ለውጦች የቴሌብር መላ አነስተኛ የብድር አገልግሎት በደንበኛዉ ተነበው ተቀባይነት ሲያገኙ (ይስማሙ የሚለውን ምርጫ ሲጫን) በደንበኛው ላይ ተፈጻሚ ይሆናሉ፡፡
1. ትርጓሜ
በዚህ የደንቦች እና ሁኔታዎች መረጃ ውስጥ የተዘረዘሩ ቃላት የሚከተለውን ትርጉም ይይዛሉ፡-
1.1. "ዳሽን ባንክ" ማለት ቁጥጥር የሚደረግበት የፋይናንስ ተቋም ሲሆን ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በመተባበር ለቴሌብር ደንበኞች መላ አነስተኛ የብድር አገልግሎት ለመስጠት የተስማማ የፋይናንስ ተቋም ነው።
1.2. "ኢትዮ ቴሌኮም" ማለት ክፍያ ለመፈፀም ፈቃድ ያለው እና ከዳሽ ባንክ ጋር በመተባበር ቴሌብር መለ አነስተኛ የብድር አገልግሎት ለቴሌብር ደንበኞች ለመስጠት ስምምነት ያለው ተቋም ነው፡፡
1.3. "የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ" ማለት በአዋጅ ቁጥር 591/2001 መሠረት ለፋይናንስ ተቋማት ፍቃድ ለመሰጠትና ሥራቸዉን ለመቆጣጠር የተቋቋመ ተቋም ነው።
1.4. "ቴሌብር" ማለት ደንበኞች የሞባይል ስልካቸዉን በመጠቀም የፋይናንስ አገልግሎቶችን ለማግኘት የሚያስችል የኢትዮ ቴሌኮም የሞባይል ገንዘብ አገልግሎት የንግድ ስም ነው።
1.5. "የቴሌብር አካውንት" ማለት የቴሌብር ተጠቃሚ ደንበኞች በኤሌክትሮኒክስ መንገድ ገንዘብ የሚያስቀምጡበት፣ የሚላላኩበት እና የሚቀበሉበት አካዉንት ነዉ ፡፡
1.6. "መላ አነስተኛ የብድር አገልግሎት" ማለት በዳሽን ባንክና በኢትዮ ቴሌኮም የጋራ ትብብር ግለሰብ ደንበኞች በኤሌክትሮኒክ ገንዘብ አነስተኛ መጠን ያለው ብድር በቴሌብር የሚያገኙበት የአገልግሎት ዓይነት ነው።
1.7. “መላ መዳረሻ አነስተኛ የብድር አገልግሎት” ማለት ለግል እና ለመንግስት ተቋማት ሰራተኞች ከየተቋማቸዉ ጋር በሚኖር ስምምነት ከታች በተቀመጡ ደንብ እና ሁኔታዎች መሰረት በቴሌብር አማካኝነት ዳሽን ባንክ ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በመተባበር የሚያቀርበዉ የብድር አገልግሎት ነው፡፡
1.8. “ግለሰብ ደንበኛ” ማለት የተፈጥሮ ሰዉ ሆኖ በስሙ የቴሌብር አካውንት ያለዉና ቴሌብር መላ አነስተኛ የብድር አገልግሎት ለመዉሰድ የተስማማ ማለት ነው።
1.9. “ኤሌክትሮኒክ ገንዘብ/ኢ- መኒ” ማለት ከ ኢትዮጵያ ብር ጋር እኩል መጠን ያለው ገንዘብን የሚወክል ደንበኛው የሚያስተዳድረዉ አና በደንበኛዉ የቴሌብር ሂሳብ ዉስጥ የሚገኝ የኤሌክትሮኒክስ የገንዘብ ዋጋ ነው።
1.10. "አንተ" ወይም " የአንተ" ማለት የግለሰብ ደንበኛ ማለት ሲሆን የግለሰቡን የግል ተወካዮችም ያጠቃልላል።
1.11. "እኛ" "አኛን" እና "የእኛ" ማለት የኢትዮጵያ ደሽን ባንክ እና ኢትዮ ቴሌኮም ማለት ነው፡፡
1.12. “የአገልግሎት ክፍያ ” ማለት መላ አነስተኛ የብድር አገልግሎትን ለመጠቀም በግለሰብ ደንበኞች የሚፈፀም ክፍያ ነው ::የዚህ ክፍያ መጠን በኢትዮ ቴሌኮም እና በዳሽን ባንክ ውሳኔ በማንኛውም ጊዜ አስቀድሞ በሚሰጥ ማሳሰቢያ ሊቀየር ይችላል።
1.13. ”ዕለታዊ ክፍያ ” ማለት ሳይከፈል በቀረዉ የዕዳ መጠን ላይ ግለሰብ ደንበኛዉ በወሰደዉ የብድር ዓየነት መሠረት በየዕለቱ የሚከፈል የክፍያ ዓይነት ነዉ ፡፡
1.14. "የቅጣት ክፍያ" ማለት የብድሩ ግለሰብ ደንበኛዉ በገባዉ ዉል መሠረት የብድሩን ገንዘብ ሳይከፍል የቀረ እንደሆን የሚከፍለዉ ገንዘብ ነዉ ፡፡
1.15. "የክፍያ ቀን " ማለት ግለሰብ ደንበኛዉ የወሰደዉን ብድር ከፍሎ እንዲያጠናቅቅ የሚጠበቅበት የመጨረሻዉ ቀን ነወ ፡፡
1.16. "የተበላሸ ብድር" ማለት ከክፍያ ቀን ማግስት ጀምሮ በሚቆጠር 90 ቀናት ዉስጥ ያልተከፈለ ዕዳ ነዉ፡፡
1.17. በአነስታይ ፆታ የተገለፁ ለተባዕታይ ፆታ እንደዚሁም በተባዕታይ ፆታም የተገለፁ ለአነስታይ ፆታ ያገለግላሉ
1.18. ግለሰብ የሚለዉ ቃል ወንድና ሴት ፆታን ለመግለፅ ያገለግላል ፡፡


2. ደንብ እና ሁኔታዎችን ስለመቀበል
2.1. መላ የብድር አገልግሎትን ለመጠቀም ከማመልከትዎ በፊት እነዚህ ደንብ እና ሁኔታዎች ላይ የተጠቀሰውን የ ብድሩን አጠቃቀም እና መመሪያ በጥንቃቄ በማንበብ እና በመረዳት መስማማት ይኖርቦታል፡፡
2.2. በእነዚህ ደንቦችና ሁኔታዎች ካልተስማሙ እባክዎን ከዝርዝር መምረጫ ውስጥ ሰርዝ የሚለውን ይጫኑ፤
2.3. ደንቦችና ሁኔታዎችን እንዳነበቡ፣ እንደተረዱና እንደተቀበሉ የሚቆጠረው፡-
“ይስማሙ” የሚለውን አማራጭ ሲጫኑ ደንብ እና ሁኔታዎችን በማንበብ ተረድተው ለማክበር መስማማትዎን እንዳረጋግጡ ወይም ብድር ክፍያን ለመጠቀም እንደተስማሙ ይወሰዳል።
2.4. መላ አነሰተኛ የብድር አገልግሎትን ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር ለመተግበር እና የክሬዲት አገልግሎትን በኤሌክትሮኒካዊ መንገድ ብቻ በቴሌብር ሲስተም ለመጠቀም ተስማምተዋል።
2.5. ደንብ እና ሁኔታዎች ከጊዜ ወደ ጊዜ በኢትዮ ቴሌኮም እና በዳሽን ባንክ ሊሻሻሉ ወይም ሊለወጡ የሚችሉ ሲሆን ይህንንም ለዉጥ የሚያስገነዝብ ማሳሰቢያ አስቀድሞ እንዲደርስዎት ይደረጋል ፡፡ እነዚህ ለዉጦች በቴሌብር ፖርታል፣በቴሌብር መተግበሪያ ወይም ድረ ገጽ ላይ ከተለቀቁበት ዕለት ጀምሮ ተግባራዊ ይደረጋሉ፡፡
2.6. ደንበኛው ገንዘቡን ለህጋዊ አላማ ለማዋል ተስማምተዋል።
3. የብድር አገልግሎትን ለማስጀመር
የብድር አገልግሎትን ከኢትዮ ቴሌኮም እና ዳሽን ባንክ ጋር ለማስጀመር ቢያንስ፡-
3.1. እነዚህን ደንቦችና ሁኔታዎችን ሊያነቡ፣ሊረዱ እና ሊስማሙ ይገባል
3.2. 18 አመት እና ከዚያ በላይ መሆን
3.3. አገልግሎት የሚሰጥ የኢትዮ ቴሌኮም ሲም ካርድ መያዝ
3.4. የቴሌብር እና የኢትዮ ቴሌኮም አገልግሎቶችን እንደ ዳታ/ድምጽ/አጭር የጽሁፍ መልዕክት የሚጠቀሙ መሆን አለብዎት
3.5. የቴሌብር የደንበኝነት ቆይታ 3 ወር እና ከዛ በላይ መሆን አለበት
ለመመዝገብ በዩ ኤስ ኤስ ዲ (*127#) ወይም በቴሌብር መተግበሪያ መጠቀም ይችላሉ፡፡
4. መላ አነሰተኛ ብድር ለማግኘት መሰረታዊ መስፈርቶች፤
• የግለሰብ ደንበኛው የመበደር አቅም፣ ደንበኛው የብድር ክፍያ አገልግሎት ለመጠቀም ጥያቄ ካቀረበበት ቀን በፊት ባደረገው የ6 ወር የቴሌብር የገንዘብ እንቅስቃሴ፣ቀደም ሲል የወሰደዉን ብድር የመክፈል ታሪክ እና በቴሌኮም አገልግሎት አጠቃቀም ይወሰናል። ከታች ያሉት የቴሌብር ግብይቶች እና የገንዘብ ልውውጥ የደንበኛ የብደር አቅምን ለማስላት ይውላሉ።
o የአየር ሰዓት መሙላት ወይም ጥቅል መግዛት (በራስ አገዝ ወይመ ከወኪሎች)፣
o ዕቃ ወይም አገልግሎት በመግዛት ግብይት መፈጸም፣
o ቢል ክፍያ (በራስ አገዝ ወይም ከወኪሎች)፣
o ለእርስዎ ወይም የሌላ ደንበኛ የፍጆታ አገልግሎት ክፍያ (በራስ አገዝ ወይም ከወኪሎች)፣
o በልክ ዲስፐርስመንት ( የቀን ሠራተኞች ክፍያ ፣ደመወዝ ፣ዕርዳታ፣ጡረታ፣…) ክፍያ በቴሌብር መቀበል፣
o ከውጭ አገር ገንዘብ መቀበል፣
o የትኬት ግዢ፣
o ለገንዘብ ማሰባሰቢያ የእርዳታ ክፍያ( ፈንድ ረይዚንግ)፣
o በቴሌብር ወኪሎች በኩል ገንዘብ መቀበልና ወጪ ማድረግ፣
o የቁጠባ አገልግሎት፣
o ገንዘብ መላክ፣
o የቴሌኮም ፍጆታ (ድምጽ፣ ዳታ ወይም መልዕክት)፣
o በቴሌብር የተወሰደን ብድር በአግባቡ የመክፈል የቀደመ ታሪክ ፡፡
• ብቁ ለመሆን ደንበኞች ከቴሌኮም አገልግሎት ፍጆታ በተጨማሪ የቴሌብር አገልግሎት መጠቀም አለባቸው፡፡
• መላ መዳረሻ ብድር ለማግኘት ወርሃዊ ደሞዝን በቴሌብር አማካኝነት መቀበል ወይም ከሚሰራበት ተቋም ጋር የሚደረግ ስምምነት በቂ ነዉ፡፡
5. የብድሩ መጠን እና ክፍያ
5.1. በሚፈቀደው ዝቅተኛ እና ከፍተኛ የብድር መጠን መካከል ማንኛውንም መጠን መበደር ይችላሉ።
5.2. የጠየቁትን የብድር መጠን እንዳገኙ የቴሌብር ሂሳብዎ (ኤሌክትሮኒክ-ገንዘብ አካውንት) ላይ ገቢ ይደረጋል።
5.3. ሌላብድር ለማግኘት መጀመሪያ ከቴሌብር የወሰዱትን ብድር መክፈል ይጠበቅብዎታል፡፡
5.4. ያለብዎትን ብድር በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ውሰጥ በከፊል ወይም በሙሉ መክፈል ይችላሉ፡፡
5.5. እንደየ ብድሩ ዐዓይነት የብድር መከክፈያ ቀነ ገደብ 1 ቀን ፣ 7 ቀን፣ 30 ቀን እና 50 ነዉ፡፡
5.6. ያለብዎትን የአንድ ቀን ዕዳ በ1 ቀን ውስጥ ከከፈሉ የዋናዉን ዕዳ 1% የአገልግሎት ክፍያ ይከፍላሉ፡፡
5.7. ያለብዎትን የሰባት ቀን ብድር በ7 ቀናት ውስጥ ከከፈሉ በመጀመሪያዉ ቀን የዋናዉን ዕዳ 1% የአገልግሎት ክፍያ እና ከሁለተኛው ቀን ጀምሮ የክሬዲት መጠነዎን መሰረት ያደረገ በቀን የዋናዉን ዕዳ ከ0.35% እስከ 1.2% ክፍያ ይከፍላሉ፡፡
5.8. ያለብዎትን ኦቨርድራፍት ብድር በ30 ቀናት ውስጥ ከከፈሉ የወሰዱትን የብድር መጠን 2.5% በመጀመሪያዉ ቀን የሚከፍሉ ሲሆን ከዚያ በኋላ ሲከፍሉ የክሬዲት መጠነዎን መሰረት ያደረገ በቀን ከ 0.3% እስከ 1.1% ተጨማሪ የአገልግሎት ክፍያ ይከፍላሉ፡፡
5.9. ያለብዎትን የሰላሳ ቀን ብድር በ30 ቀናት ውስጥ ከከፈሉ የወሰዱትን የብድር መጠን 3% በመጀመሪያዉ ቀን የሚከፍሉ ሲሆን ከዚያ በኋላ ሲከፍሉ የክሬዲት መጠነዎን መሰረት ያደረገ በቀን ከ0.3% እስከ 0.8% ተጨማሪ የአገልግሎት ክፍያ ይከፍላሉ፡፡
5.10. ያለብዎትን የሃምሳ ቀን ብድር በ50 ቀናት ውስጥ በትክክል ከከፈሉ የአገልግሎት ክፍያ የወሰዱትን የብድር መጠን 6% የሚከፍሉ ሲሆን ከዚያ በኋላ ሲከፍሉ የክሬዲት መጠነዎን መሰረት ያደረገ በቀን ከ0.5% እስከ 0.7% ተጨማሪ የአገልግሎት ክፍያ ይከፍላሉ፡፡
5.11. ለመላ መዳረሻ የብድር ክፍያዉ በወሰዱት የብድር ጊዜ ተከፋፍሎ ቀስ በቀስ ይከፈላል ፡፡
5.12. የደመወዝዎን 30% ለወሰዱት መላ መዳረሻ የመክፈያ ቀነ ገደቡ 3 ወር ሲሆን 10% የአገልግሎት ክፍያ ይከፍላሉ፡፡
5.13. የመክፈያ ጊዜዉ 9 ወር ለሆነ የ2 ወር ደመወዝ መላ መዳረሻ ብድር 16% የአገልግሎት ክፍያ ይከፍላሉ ፡፡
5.14. የመክፈያ ጊዜዉ 12 ወር ለሆነ የ3 ወር ደመወዝ መላ መዳረሻ ብድር 20% የአገልግሎት ክፍያ ይከፍላሉ ፡፡
5.15. የ2 እና የ3 ወር መላ መዳረሻ ብድርን ከመክፈያ ጊዜዉ ቀደም ብሎ ከከፈሉ የቀሪ ክፍያዉን 3% ብቻ የአገልግሎት ክፍያ ይከፍላል፡፡
5.16. ያለብዎትን ዕዳ በቀነ ገደቡ ውስጥ የማይከፍሉ ከሆነ ባለበዎት ክሬዲት መጠን ላይ በየዕለቱ የሚሰላ 0.11% የቅጣት ክፍያ ይከፍላሉ፡፡ ነገር ግን ለመላ የቀን ብድር ያለብዎን ክሬዲት በቀነ ገደቡ ውስጥ የማይከፍሉ ከሆነ ባለበዎት ክሬዲት መጠን ላይ በየዕለቱ የሚሰላ 2% የቅጣት ክፍያ ይከፍላሉ::
5.17. ብደሩን የመክፈያ ቀነ ገደብ ባለፈ 90 ቀናት ዉስጥ ግለሰብ ደንበኛዉ የማይከፍል ከሆነ ሳይከፈል የቀረዉ ዕዳ ከሳንዱቅ የቁጠባ ሂሳቡ በቀጥታ ተቆራጭ ይደረጋል፣
5.18. በጉርሻ የሚያገኙት ገንዘብ ለክሬዲት ክፍያ አይውልም፡፡
5.19. ብድሩ መከፈል ባለበት ጊዜ ሳይከፈል የቀረ እንደሆነ ኢትዮ ቴሌኮም እና ዳሽን ባንክ አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ ከባለዕዳዉ የደሽን ባንክ ወይም ሌሎች ባንኮች ሒሳብ በቀጥታ መቁረጥን ጨምሮ ማናቸዉም አማራጭ ዜዴዎች በመጠቀም ከፍርድ ቤት ዉጭ ባለ አማራጭ ዕዳዉን መሰብሰብ ይችላሉ፡፡
5.20. የመክፈያ ጊዜው ካለፈ በኋላ ግለሰብ ደንበኛዉ በሰዓቱ ካልከፈለ ኢትዮ ቴሌኮም እና ዳሽን ባንክ የቀረውን የብድር መጠን ከቴሌብር ሂሳቡ ወዲያውኑ ተቀናሽ ያደርጋሉ ፡፡
5.21. ከፍርድ ቤት ዉጭ ባለ አማራጭ ዕዳዉን ለመሰብሰብ ያግዝ ዘንድ ኢትዮ ቴሌኮም እና ዳሽን ባንክ የግለሰብ ደንበኛዉን የመኖሪያ ወይም የሥራ አድራሻ ማናቸዉም አማራጭ ዘዴዎች በመጠቀም አፈላልገዉ በማግኘት ዕዳዉን የመሰብሰብ መብት ያላቸዉ መሆኑን ግለሰብ ደንበኛዉ ተስማምቷል፡፡
5.22. ዕዳዉ መከፈል ባለበት ጊዜ ሳይከፍል የቀረ እንደሆነ ኢትዮ ቴሌኮም እና ዳሸን ባንክ የግለሰብ ደንበኛዉን የግል መረጃ ዕዳዉን በመሰብሰብ ሥራ ላይ ለሚሳተፍ ሦስተኛ ወገን (ድርጅት ወይም ግለሰብ) አሳልፈዉ መስጠት የሚችሉ መሆኑን ግለሰብ ደንበኛዉ ተስማምቷል፡፡
5.23. ከፍርድ ቤት ዉጭ ባለ አማራጭ ዕዳዉ የማይከፈል ከሆነ ኢትዮ ቴሌኮም እና ዳሽን ባንክ ጉዳዩን ወደ መደበኛ ፍርድ ቤት በራሳቸዉ ወይም በሌላ የሕግ አገልግሎት ሰጪ ተቋም ወይም በግለሰብ ጠበቃ አማካኝነት የመውሰድና የመክሰስ ሙሉ መብት አላቸው፡፡
6. ተፈጻሚነት ያለው ህግ
የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕጎች፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ መመሪያዎች፣ እንዲሁም የዳሽን ባንክና የኢትዮ ቴሌኮም አግባብነት ያላቸው አሠራሮች በእነዚህ ደንብ እና ሁኔታዎች ላይ ተፈጻሚ ይሆናሉ፡፡
7. መረጃ ስለመጠየቅ
ከቴሌብር መላ አገልግሎት፣ ሂደት፣ ደንብ እና ሁኔታዎች ጋር ለተያያዘ ማንኛውም ጥያቄ በቴሌብር የደንበኞች ግንኙነት ማእከል (127 በመደወል) ተጨማሪ መረጃ ማግኘት ይችላሉ።
8. የውል መቋረጥ
ማንኛውንም የአነስተኛ ቁጠባ እና ብድር አገልግሎቶችን ያለቅድመ ማስጠንቀቂያ ወይም ያለማስታወቂያ በእርስዎ አላግባብ መጠቀም ወይም ማጭበርበር ምክንያት ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል ለማገድ ወይም ለማቋረጥ መብት ይኖረናል። የዚህ ውል መቋረጥ ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የሁለቱም ተዋዋይ ወገኖች መብቶችን እና ግዴታዎችን ሊነካ አይችልም።


9. ቅሬታዎች
ቅሬታዎች በአካል፣ በጽሁፍ፣ በፖስታ፣ በፋክስ፣ በኢሜል ወይም በስልክ ሊቀርቡ ይችላሉ። ኢትዮ ቴሌኮም ቅሬታዎን በተገቢው ጊዜ ለመፍታት ሁሉንም እርምጃዎች ይወስዳል። በመልሱ ካልረኩ ጉዳዩን ወደ ዳሽን ባንክ እና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በቅደም ተከተል መውሰድ ይችላሉ::
10. የግጭት አፈታት
ከዚህ ውል ጋር በተያያዘ የሚነሳ ማንኛውም አለመግባባት ከላይ በአንቀጽ 9 መሠረት ያልተፈታ እንደሆነ ስልጣን ላለው የኢትዮጵያ ፌዴራል ፍርድ ቤት መቅረብ ይችላል።
11. የመያዝ መብት
እኛ ጋር ያለብወትን እዳ ካልከፈሉ በተለይም በጥሬ ገንዘብ፣ዕቃዎች፣ዋስትናዎች፣ውድ ጌጦች፣ቼኮች እና ማንኛውን ተንቀሳቃሽም ሆነ የማይነቀሳቀስ ንብረትዎ ላይ አጠቃላይ የመያዝ መብት ይኖረናል፡፡እኛ ጋር ያለቦትን እዳ መክፈል የማይችሉ ከሆነ እና የማቻቻል መብት ሲፈጠር በመያዣ መብት ስር የተያዙ ንብረቶችን ላልተከፈለው ብድር እንደ ዋስትና ተደርጎ መቁጠር ይቻላል፡፡

12. ዕዳ ስለማቻቻል
የወሰዱትን አነስተኛ ብድር መጠን እንዲከፍሉ ካሳወቅን በኋላ በተቀመጠለት ጊዜ ገደብ ውስጥ መመለስ ካልቻሉ ባንክ ውስጥ ካሉዎት ሌሎች የባንክ ተቀማጭ ጥሬ ገንዘብ፣ ቁጠባ፣ተርም ዲፖዚት፣የጋራ ወይም የተናጠል ከሆኑት ላይ ያለበዎትን ክሬዲት መጠን ያህል ለመውሰድ እንችላለለን ፡፡
13. ማስተባበል
የቴሌብር ሚስጥር ቁጥር (ፒን) በሚስጥር መቀመጥ አለበት ከእርስዎ ሌላ ለማንም ተደራሽ መሆን የለበትም። የሚስጥር ቁጥርዎን ሌላ ሶስተኛ ወገን እንዲያዉቀዉ በማድረግዎ ወይም በየጊዜው ባለመቀየርዎ፣ ያልተፈቀደ የቴሌብር አጠቃቀም በማከናወንዎ፣ የሞባይል ስልክዎ ወይም ሲም ካርድ ሲሰረቅብዎ ወይም ሲጠፋብዎ ለሚመለከተዉ አካል ፈጥነዉ ባለማሳቅዎ እና ባለመስዘጋትዎ የሚደርስብዎ ኪሳራ /ጉዳት የእርስዎ ኃላፊነት ብቻ ይሆናል፡፡