መላ (አነስተኛ ብድር)

ይህ የአገልግሎት አይነት ለግለሰብ እና ለነጋዴዎች/ወኪሎች አነስተኛ ንግድ/ቢዝነስ እንዲጀምሩ ወይም እንዲያስፋፉ በኤሌክትሮኒክ ገንዘብ አነስተኛ መጠን ያለው ክሬዲት የሚያገኙበት የአገልግሎት አይነት ነው።

ለመላ ክሬዲት ተለዋዋጭ ዋጋ

 ሳምንታዊ
ወርሃዊ
የብድር መጠን አገልግሎቱን ለማግኘት የሚከፈል እለታዊ ክፍያ እለታዊ የቅጣት ክፍያ
የብድር መጠን አገልግሎቱን ለማግኘት የሚከፈል እለታዊ ክፍያ እለታዊ የቅጣት ክፍያ
ትንሹ የመጨረሻው
ትንሹ የመጨረሻው
100 5000 1% 0.35% 0.50%
100 10000 3% 0.35% 0.50%
4000 0.40%
8000 0.40%
3000 0.85%
6000 0.65%
2000 1.05%
2500 0.85%
1000 1.10%
1000 1.05%
100 1.20%
200 1.20%

መዳረሻ

መዳረሻ የቴሌብር መላ አገልግሎት አንዱ አካል ሲሆን በቴሌብር ደሞዛቸውን ለሚቀበሉ የመንግስት እና የግል ሰራተኞች ክሬዲት እንዲያገኙ የሚያስችል አገልግሎት ነው፡፡

                          መላ መዳረሻ

ምርት

ዝቅተኛ

ከፍተኛ

የአገልግሎት ክፍያ

የክሬዲት መጠን

1000

36000

 

የመመለሻ ቀነ ገደብ

90 ቀናት ወይም 3 ወር

 

 

የብድር መክፈያ ጊዜ

በየወሩ

 

 

ከመመለሻ ቀነ ገደብ ወይም 90 ቀናት በኋላ

 

0.5%  በቀን

 

ማስታወሻ፡

  • የብድር ገደብ ከብር 1,000 እስከ 36,000 ነው።
  • የመመለሻ ቀነ ገደብ ከ90 ቀናት በኋላ ይሆናል….

መላ መዳረሻቴሌብር መተግበሪያ አገልግሎት ለመጠቀም

  1. የፋይናንስ አገልግሎትን ይምረጡ
  2. ቴሌብር መላን ይምረጡ
  3. መላ መዳረሻን ይምረጡ
  4. ክሬዲት ገደብዎን ይመልከቱ
  5. ክሬዲት ይጠይቁ የሚለውን
  6. የብር መጠን አስገብተው ይመልከቱ የሚለውን ይጫኑ
  7. ለመጨረስ ያረጋግጡ የሚለውን ይጫኑ

በአጭር ቁጥር *127# በመደወል

  1. *127# ይደውሉ
  2. ለፋይናንሽያል አገልግሎት 1ን ያስገቡ
  3. ለቴሌብር መላ 1ን ያስገቡ
  4. ክሬዲት ለመውሰድ 1ን ይምረጡ
  5. ወደ ቀጣይ ማውጫ ለመሄድ (#) ን ቀጥሎ መዳረሻ 3 ወርን ለመምረጥ 4ን ያስገቡ
  6. በቀጣይ ማውጫ (#) የሚፈልጉትን የክሬዲት መጠን ያስገቡ
  7. ለማረጋገጥ 1ን ያስገቡ

  • የመዳረሻ ክሬዲት አገልግሎትን ለማግኘት ሰራተኞች በቅድሚያ የውል ስምምነት መፈጸም ይገባቸዋል፡፡
  • ሰራተኞች በ90 ቀናት ውስጥ ብድሩን ከመለሱ የአገልግሎት ክፍያው 10% ይሆናል።
  • ከብድር መክፈያ ቀነ ገደቡ በኋላ ተበዳሪዎች በቀን5% ከጠቅላላው ቀሪ ክፍያ እንዲከፍሉ ይደረጋል።
  • ደመወዛቸው በቴሌብር ገቢ ሲደረግ የተመላሽ ክፍያው ወዲያውኑ ተቀናሽ/ተፈጻሚ ይሆናል።
  • ሰራተኞች የደሞዛቸውን 30% መበደር ይችላሉ።
  • ከፋይ/ቀጣሪ ድርጅቱ እና እና ሰራተኞች ደሞዛቸውን በቴሌብር ለመቀበል የሚያስችል ስምምት ማድረግ ይገባቸዋል፡፡
  • የመዳረሻ ብድር አገልግሎትን ለማግኘት ሰራተኞች 3 ጊዜ (ወራት) ደሞዛቸውን በቴሌብር መቀበል ይጠበቅባቸዋል።
  • የኮንትራት ውሉ ሲፈረም የደመወዛቸውን 30% በክሬዲት እንዲወስዱ የሚያስችል ይሆናል።
  • ክሬዲቱ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ የሚከፈል ይሆናል፡፡
  • ቀጣሪ ድርጅቱ/ኩባንያው የሰራተኞቹ የደሞዝ ክፍያ በቴሌብር መክፈሉን እንደሚቀጥል በማረጋገጥ እንንሁም ኮንትራቱን ሲያቋርጥ ከአንድ ወር በፊት ለኢትዮ ቴሌኮም ማሳወቅ አለበት።

የቴሌብር መላ አገልግሎት ለማግኘት ብቁ የሚያደርጉ መስፈርቶች

  • የደንበኛ የመበደር አቅም ደንበኛው ባደረገው የ6 ወር የቴሌብር የገንዘብ እንቅስቃሴ እና በቴሌኮም አጠቃቀም ይወሰናል።
  • በተጨማሪም ከታች ያሉት የቴሌብር ግብይቶች እና የገንዘብ ልውውጥ የደንበኛ የብድር አቅምን ለማስላት የሚውሉ ይሆናል።
    • ለእርስዎ ወይም በስጦታ የአየር ሰዓት መሙላት ወይም ጥቅል
      መግዛት (በራስ አገዝ ወይም ከወኪሎች)
    • ዕቃ ወይም አገልግሎት ግዢን መፈጸም
    • ለእርስዎ ወይም የሌላ ደንበኛ ቢል ክፍያ (በራስ አገዝ ወይም
      ከወኪሎች) ማከናወን
    • ለእርስዎ ወይም የሌላ ደንበኛን የፍጆታ አገልግሎት ክፍያ (በራስ አገዝ ወይም ከወኪሎች) መፈፀም
    • ከውጭ አገር ገንዘብ መቀበል
    • የጅምላ ክፍያ (ደሞዝ፣ ሴፍቲኔት…) መፈፀም 
    • የትኬት ክፍያ መፈፀም
    • ለገንዘብ ማሰባሰቢያ የእርዳታ ክፍያ መፈፀም
    • የቁጠባ አገልግሎት
    • የቴሌኮም ፍጆታ (ድምጽ፣ ዳታ ወይም መልዕክት) መፈፀም

• ከቴሌኮም አገልግሎት ፍጆታ በተጨማሪ ቢያንስ አንድ የቴሌብር አገልግሎት መጠቀም ይኖርብዎታል፡፡
• የ6 ወራት ግብይት ወይም አጠቃቀም ለብቁነት መስፈርት የሚቆጠር ይሆናል።
• በሚፈቀደው ዝቅተኛ እና ከፍተኛ የክሬዲት መጠን መካከል ማንኛውንም መጠን መበደር ይችላሉ።

የቴሌብር መላ አገልግሎት ለማግኘት ብቁ የሚያደርጉ መስፈርቶች

  • 18 አመት እና ከዚያ በላይ
  • አገልግሎት የሚሰጥ የኢትዮ ቴሌኮም ሲም ካርድ መያዝ
  • የቴሌብር እና የኢትዮ ቴሌኮም አገልግሎቶችን እንደ ዳታ/ድምጽ/አጭር የጽሁፍ መልዕክት መጠቀም ይኖርብዎታል፡፡
  • ለመመዝገብ በአጭር ቁጥር (*127#) ወይም በቴሌብር መተግበሪያን ይጠቀሙ፡፡
  • የቴሌብር የደንበኝነት ቆይታ 3 ወር እና ከዛ በላይ መሆን ይኖርበታል፡፡

በቴሌብር
የሞባይል መተግበሪያ
እንዴት አገልግሎቱን ማስጀመር እና መጠቀም እችላለሁ?

አገልግሎቱን ለማስጀመር

  • የፋይናንስ አገልግሎት የሚለውን ይጫኑ
  • ቴሌብር መላ የሚለውን ይምረጡ _ ደንብ እና ሁኔታዎችን በማንበብ የ √ ምልክት በመጫን መስማማትዎን ይግለጹ
  • ለማስጀመር የሚለውን ይጫኑ

ክሬዲት ለመውሰድ

  • ቴሌብር መላ ከሚለው ስር የሚፈልጉትን ኮንትራት ይምረጡ
  • የክሬዲት ገደብዎን እና የክሬዲቱን ዝርዝር ደንቦች ይመልከቱ
  • ክሬዲት ይጠይቁ የሚለውን ይምረጡ
  • የክሬዲት መጠን ያስገቡ
  • ይመልከቱ የሚለውን ይጫኑ
  • ያረጋግጡ የሚለውን በመጫን ይጨርሱ

ክሬዲት ለመክፈል

  • ቴሌብር መላ ከሚለው ስር የእኔ ቴሌብር መላ የሚለውን ይምረጡ
  • የሚከፍሉትን ኮንትራት ይምረጡ
  • በውል ዝርዝር ስር ይክፈሉ የሚለውን ይጫኑ
  • የሚከፍሉትን የብር መጠን ያስገቡ (በሙሉ ወይም በከፊል)
  • ያረጋግጡ የሚለውን በመጫን ይጨርሱ

ለግለሰብ ደንበኞች

  • 18 ዓመት እና ከዚያ በላይ ዕድሜ፣
  • ደንበኛው በስድስት ወራት ውስጥ ያከናወናቸው ግብይቶች ማለትም
    • የአየር ሰዓት እና ጥቅል መግዛት፣
    • የኢትዮ ቴሌኮም አገልግሎቶች (ድምጽ፣ አጭር ጽሁፍ እና ዳታ) አጠቃቀም፣
    • የኢትዮ ቴሌኮም ኔትዎርክ የቆይታ ጊዜ፣
    • ምርቶችንና አገልግሎትን መግዛት፣ ወርሃዊ የአገልግሎት ክፍያዎችን መፈጸም፣
    • የገቢ ማሰባሰቢያ ክፍያ፣
    • ገንዘብ ለመላክ፣
    • ገንዘብ ተቀማጭ ማድረግ፣
    • ገንዘብ ወጪ ማድረግ፣
    • ከውጭ ሃገር ገንዘብ መቀበል፣
    • በአንዴ ብዙ ክፍያዎን መፈጸም (ደመወዝ፣ ሴፍቲኔት..)፣
    • ትኬት መግዛት፣
    • ከዚህ በፊት የነበር የብድር ታሪክ፣ ወዘተ ግምት ውስጥ የሚገቡ ይሆናል፡፡
  • ደንበኛው ከዚህ በፊት የወሰደውን አነስተኛ ብድር ካልመለስ መበደር አይችልም፡፡
  • የአነስተኛ ብድር፣ የአየር ሰዓት ብድር እና የኢትዮ ቴል አገልግሎት ብድር ያለበት ደንበኛ ለአስተኛ ብድር አገልግሎት ብቁ አይሆንም፡፡

ለነጋዴዎች ወይም ወኪሎች

ሀ. ወኪል

    • ወኪሉ ለብድር አገልግሎቱ ተጨማሪ የውል ስምምነት መፈጸም ይኖርበታል፣
    • ወኪሉ ባለፉት ሶስት ወራት ውስጥ በቴሌብር ጥሩ የስራ እንቅስቃሴ ያለው፣
    • በተጨማሪም የጥቅል ሽያጭ፣ ወርሃዊ የአገልግሎት ክፍያ መፈጸም፣ ገንዘብ ወጪ ማድረግ፣ የአየር ሰዓት መሙላት፣ ለቴሌብር አገልግሎት የተመዘገቡ ደንበኞች ብዛት እና የደንበኝነት ደረጃ ማሳደግ፣ የብድር መመለስ ሁኔታ ግምት ውስጥ የሚገቡ ይሆናል፡፡

ለ. ነጋዴ

    • ለብድር አገልግሎቱ ተጨማሪ የውል ስምምነት መፈጸም እንዲሁም የታደሰ ንግድ ፍቃድ እና የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ማቅረብ።
    • ነጋዴው ባለፉት ሶስት ወራት ውስጥ በቴሌብር ጥሩ የስራ እንቅስቃሴ ያለው እንዲሁም በቴሌብር ክፍያዎችን የተቀበለ፣ በቴሌብር ምርትና አገልግሎቶችን የሸጠ፣ የአየር ሰዓት የሞላ መሆን ይገባዋል፡፡
    • በተጨማሪም የወሰዱትን ብድር በቶሎ መመለስ በድጋሚ ለመበደር ያስችላል፡፡
    1.  

 የውል ስምምነት

  1. ይህ ስምምነት (ከዚህ በኋላ "ደንቦች እና ሁኔታዎች" የሚባል) የቴሌብር መላ የክሬዲት አገልግሎትን በተመለከተ አጠቃላይ ደንብ እና ሁኔታዎች ያካትታል፡፡
  2. እነዚህ ደንቦችና ሁኔታዎች እንዲሁም ከዚህ ጋር የተያያዙ ማሻሻያዎች እና ለውጦች በክሬድት ደንበኛው ተነበው ተቀባይነት ሲያገኙ (ይሲማሙ የሚለውን ምርጫ ሲጫኑ) ሥራ ላይ ይውላሉ፡፡
  3. ትርጓሜ

በዚህ የደንቦች እና ሁኔታዎች መረጃ ውስጥ የተዘረዘሩ ቃላት እና አባባሎች የሚከተለውን ትርጉሜ ይይዛሉ፡-

  • "የቴሌብር መላ የክሬዲት አገልግሎት" ማለት ለግለሰብ አነስተኛ ንግድ/ቢዝነስ እንዲጀምሩ ወይም እንዲያስፋፉ በኤሌክትሮኒክ ገንዘብ አነስተኛ መጠን ያለው ክሬዲት የሚያገኙበት የአገልግሎት አይነት ነው።
  • “የቴሌብር መላ መዳረሻ ክሬዲት አገልግሎት” ማለት ወርሃዊ ደመወዛቸውን በቴሌብር አገልግሎት ለሚከፈላቸው የግል እና የመንግስት ተቋማት ሰራተኞች ከታች በተቀመጡ ደንብ እና ሁኔታዎች መሰረት በኢትዮ ቴሌኮም የቴሌብር አገልግሎት በዳሽን ባንክ የሚቀርብ የክሬዲት አገልግሎት ነው፡፡
  • “የክሬዲት አገልግሎት” ማለት ከታች በተቀመጡ ደንብ እና ሁኔታዎች መሰረት በኢትዮ ቴሌኮም የቴሌብር አገልግሎት በዳሽን ባንክ ለግለሰብ ደንበኞች የሚቀርብ የክሬዲት አገልግሎት ነው፡፡
  • “የግለሰብ ደንበኛ” ማለት በስሙ በቴሌብር አካውንት የቴሌብር መላ ክሬዲት አገልግሎት የተመዘገበ ደንበኛ ማለት ነው።
  • “ኢ-ገንዘብ” ማለት እኩል መጠን ያለው ጥሬ ገንዘብን የሚወክል ደንበኛው የሚመለከተው የቴሌብር የኤሌክትሮኒክስ የገንዘብ ዋጋ ነው።
  • "የማስተላለፊያ ክፍያዎች" ማለት አነስተኛ የብድር አገልግሎት በሚጠቀሙበት ጊዜ የሚከፈሉ የአገልግሎት ክፍያዎች፣ ቅጣቶች እና ሌሎች ክፍያዎች ማለት ነው። የዝውውር ዋጋ በኢትዮቴሌኮም ውሳኔ በማንኛውም ጊዜ ሊቀየር ይችላል።

 

 

  • “የአገልግሎት ክፍያ” ማለት የክሬዲት ክፍያ አገልግሎትን ለመጠቀም በደንበኞች የሚከፈል የክፍያ መጠን ነው።
  • "የቅጣት ክፍያ" ማለት ለክሬዲት የመጨረሻ መክፍያ ቀነ ገደቡ አልፎ ክፍያው ሲፈጸም የሚከፍል ተጨማሪ የክፍያ መጠን ነው፡፡
  • "የመጨረሻ ክፍያ ቀን" ማለት የክሬዲት መመለሻ የጊዜ ገደብ (ገባሪ የክሬዲት ጊዜ) ያላለፈ መሆኑን የሚያሳይ ሲሆን ክሬዲት ከተሰጠበት ቀን ጀምሮ ያሉትን 1፡ 7 እና 30 ቀናትን የሚያካትት ነው፡፡
  • "ቀነ ገደቡ ያለፈ" ማለት የክሬዲት መመለሻ ቀነ ገደቡ ያለፈ መሆኑን የሚያሳይ ነው፡፡
  • "የተበላሸ ብድር" ማለት ክሬዲት ከተሰጠበት ቀን ጀምሮ በ90 ቀናት ውስጥ ያልተከፈለ ክሬዲት ሲሆን በወቅቱ ባለመመለሱ እንደ ተበላሸ ብድር መሆኑን የሚያሳይ ጊዜ ነው፡፡
  1. ደንብ እና ሁኔታዎችን ስለመቀበል
  • የቴሌብር መላ የክሬዲት አገልግሎትን ለመጠቀም ከማመልከትዎ በፊት እነዚህን ደንብ እና ሁኔታዎች በጥንቃቄ በማንበብ የክሬዲት አጠቃቀም እና መመሪያን አንብበው ይስማሙ፡፡
  • በእነዚህ ደንቦችና ሁኔታዎች ካልተስማሙ እባክዎን ከዝርዝር መምረጫ ውስጥ ሰርዝ የሚለውን ይጫኑ፤
  • ደንቦችና ሁኔታዎችን እንዳነበቡ፣ እንደተረዱና እንደተቀበሉ የሚቆጠረው፡-
  • “ይስማሙ” የሚለውን አማራጭ ሲጫኑ ደንብ እና ሁኔታዎችን በማንበብ ተረድተው ለማክበር መስማማትዎን እንዳረጋግጡ ወይም ክሬዲት ክፍያን ለመጠቀም እንደተስማሙ ይወሰዳል።
  • ደንብ እና ሁኔታዎች ከጊዜ ወደ ጊዜ በኢትዮ ቴሌኮም እና በዳሽን ባንክ ሊሻሻሉ ወይም ሊለወጡ የሚችሉ ሲሆን በቴሌብር ፖርታል፣በቴሌብር መተግበሪያ ወይም ድህረ ገጽ ላይ ከተለቀቁበት ዕለት ጀምሮ በደንበኛው ላይ ተግባራው ይደረጋሉ፡፡
  • የክሬዲት ክፍያ አገልግሎትን በኤሌክትሮኒካዊ መንገድ ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር ለመተግበር እና የክሬዲት ክፍያ አገልግሎትን በኤሌክትሮኒካዊ መንገድ በቴሌብር ሲስተም ለመጠቀም ተስማምተዋል።
  • ደንበኛው ገንዘቡን ለህጋዊ አላማ ለማዋል የተስማማ መሆኑን ተስማምተዋል።
  1. የክሬዲት አገልግሎትን ለማስጀመር
  • የክሬዲት አገልግሎትን ከኢትዮ ቴሌኮም እና ዳሽን ባንክ ጋር ለማስጀመር ቢያንስ፡-
  • 18 አመት እና ከዚያ በላይ

 

  • አገልግሎት የሚሰጥ የኢትዮ ቴሌኮም ሲም ካርድ መያዝ
  • የቴሌብር እና የኢትዮ ቴሌኮም አገልግሎቶችን እንደ ዳታ/ድምጽ/አጭር የጽሁፍ መልዕክት የሚጠቀሙ
  • የቴሌብር የደንበኝነት ቆይታ 3 ወር እና ከዛ በላይ መሆን አለበት
  • ለመመዝገብ በዩኤስኤስዲ (*127#) ወይም በቴሌብር መተግበሪያ መጠቀም ይችላሉ፡፡
  • ለተሳካ ምዝገባ የማሳወቂያ አጭር የፅሁፍ መልዕክት ይደርስዎታል፡፡
  1. የቴሌብር መላ የክሬዲት አገልግሎት ለማግኘት መሰረታዊ መስፈርቶች
  • የደንበኛ የመበደር አቅም ደንበኛው የክሬዲት ክፍያ አገልግሎት ለመጠቀም ጥያቄ ካቀረበበት ቀን በፊት ባደረገው የ6 ወር የቴሌብር የገንዘብ እንቅስቃሴ እና በቴሌኮም አጠቃቀም ይወሰናል። ከታች ያሉት የቴሌብር ግብይቶች እና የገንዘብ ልውውጥ የደንበኛ የብደር አቅምን ለማስላት ይውላሉ።
    • ለእርስዎ ወይም ለስጦታ የአየር ሰዓት መሙላት ወይም ጥቅል መግዛት (በራስ አገዝ ወይመ ከወኪሎች)
    • ዕቃ ወይም አገልግሎት በመግዛት ግብይት መፈጸም
    • ለእርስዎ ወይም የሌላ ደንበኛ ቢል ክፍያ (በራስ አገዝ ወይም ከወኪሎች)
    • ለእርስዎ ወይም የሌላ ደንበኛ የፍጆታ አገልግሎት ክፍያ (በራስ አገዝ ወይም ከወኪሎች)
    • ከውጭ አገር ገንዘብ መቀበል
    • የጅምላ ክፍያ (ደሞዝ፣ ሴፍቲኔት…)
    • የትኬት ክፍያ
    • ለገንዘብ ማሰባሰቢያ የእርዳታ ክፍያ
    • የቁጠባ አገልግሎት
    • ገንዘብ መላክ
    • የቴሌኮም ፍጆታ (ድምጽ፣ ዳታ ወይም መልዕክት)
  • ብቁ ለመሆን ደንበኞች ከቴሌኮም አገልግሎት ፍጆታ በተጨማሪ የቴሌብር አገልግሎት መጠቀም አለባቸው፡፡
  • መላ መዳረሻ ክሬዲት ለማግኘት ወርሃዊ ደሞዝን በቴሌብር አማካኝነት መቀበል በቂ ነው፡፡
  1. የክሬዲት መጠን እና ክፍያ
  • በሚፈቀደው ዝቅተኛ እና ከፍተኛ የክሬዲት መጠን መካከል ማንኛውንም መጠን መበደር ይችላሉ።
  • የጠየቁትን የብድር መጠን እንዳገኙ በዋናው የቴሌብር ሂሳብዎ (ኤሌክትሮኒክ-ገንዘብ አካውንት) ላይ ገቢ ይደረጋል።
  • ሌላ ክሬዲት ለማግኘት መጀመሪያ ቀድመው የወሰዱትን ክሬዲት መክፈል ይጠበቅብዎታል፡፡
  • ያለብዎትን ክሬዲት በከፊል ወይም በሙሉ መክፈል ይችላሉ።
  • የክሬዲት መክፈያ ማብቂያ ቀነ ገደብ ብድሩን ከወሰዱበት ቀን ጀምሮ በሚቆጠር እንደ ብድር አይነቱ 1ቀን፣7ቀን እና 30 ቀናት ውስጥ ይሆናል።
  • ያለብዎትን የአንድ ቀን ክሬዲት በ1 ቀን ውስጥ ከከፈሉ 1% የአገልግሎት ክፍያ ይከፍላሉ ፡፡
  • ያለብዎትን የሰባት ቀን ክሬዲት በ7 ቀናት ውስጥ ከከፈሉ 1% የአገልግሎት ክፍያ እና ከሁለተኛው ቀን ጀምሮ የክሬዲት መጠነዎን መሰረት ያደረገ በቀን ከ0.35% እስከ 1.2% ክፍያ ይከፍላሉ ፡፡
  • ያለብዎትን የሰላሳ ቀን ክሬዲት በአንድ ቀን ውስጥ ከከፈሉ የወሰዱትን የብድር መጠን 3% ሲሆን ከዚያ በኋላ ሲከፍሉ የክሬዲት መጠነዎን መሰረት ያደረገ በቀን ከ0.3% እስከ 1.2% ተጨማሪ የአገልግሎት ክፍያ ይከፍላሉ፡፡
  • በአንድ ጊዜ የተወሰደ የመላ መዳረሻ ክሬዲት በሶስት ተከታታይ ወራት ውስጥ መከፈል አለበት፡፡ ለሶስት ወር ተሰልቶ የተቀመጠው የክሬዲት መጠን በትክክል በሶስት ወር ከተከፈለ አስር በመቶ (10%) የአገልግሎት ክፍያ ይጠየቃል፡፡
  • ያለብዎን ክሬዲት በቀነ ገደቡ ውስጥ የማይከፍሉ ከሆነ ባለበዎት ክሬዲት መጠን ላይ በየዕለቱ የሚሰላ 0.5% የቅጣት ክፍያ ይከፍላሉ፡፡ ነገር ግን ለመላ የቀን ብድር ያለብዎን ክሬዲት በቀነ ገደቡ ውስጥ የማይከፍሉ ከሆነ ባለበዎት ክሬዲት መጠን ላይ በየዕለቱ የሚሰላ 2% የቅጣት ክፍያ ይከፍላሉ፡፡
  • ከብድሩ ቀነ ገደብ በኋላ ያልተመለሰ ክሬዲት መጠን ከቴሌብር ሂሳብ ወዲያውኑ ተቀናሽ ይደረጋል፡
  • በጉርሻ የሚያገኙት ገንዘብ ለክሬዲት ክፍያ አይውልም፡፡
  • ይህ የክሬዲት አገልግሎት የሚሰጠው ኢትዮ ቴሌኮም ከዳሸን ባንክ ጋር በመተባበር ነው፡፡ ለክሬዲት አገልግሎት የሚውለውን ገንዘብ የሚያቀርበው ዳሸን ባንክ ሲሆን ይህን ገንዘብ በባለቤትነት የሚቆጣጠረው ዳሸን ባንክ ነው፡፡ የተበላሸ ወይም ቀነ ገደቡ ያለፈ ብድር በሚከሰትበት ጊዜ ባንኩ ጉዳዩን ወደ መደበኛ ፍርድቤት የመውሰድና የመክሰስ ሙሉ መብት አለው፡፡ ያለብዎትን እዳ ከዳሸን ባንክ የተቀማጭ ሂሳብዎ ላይ መቁረጥን ጨምሮ ከፍርድቤት ውጭ ያሉ አማራጮች የመጠቀም መብት አለው፡፡