ደንብና ሁኔታዎች

ከውጭ ሀገራት የአየር ሰዓት እና ጥቅል ለሚቀበሉ ደንበኞቻችን ከዚህ በታች የተጠቀሱት ዝርዝር ደንብና ሁኔታዎች ተፈፃሚ ይሆናሉ፡፡

    • ከ99 ብር ጀምሮ የአየር ሰዓት እንዲሁም የሞባይል ጥቅል ስጦታ ከውጭ ሃገራት ሲቀበሉ የተቀበሉትን 10% በስጦታ ያገኛሉ
    • ስጦታው የሚያገለግለው ለ30 ቀናት ብቻ ነው፡፡
    • ስጦታውን ለቴሌኮም ፍጆታ ማለትም ለመደወል፣ መልዕክት ለመላክ እና ዳታ ለመጠቀም ወይም ለራስዎ ጥቅል በመግዛት መጠቀም ያስችላል፡፡
    • ስጦታውን ወደ ሌላ ደንበኛ ማስተላለፍ አይችሉም
    • በስጦታው ወደ አጭር ቁጥር ለመደወል፣ ዓለም አቀፍ ጥሪ ለማድረግ፣ ለሮሚንግ አገልግሎት ለመጠቀም፣ ለሌላ ደንበኛ ጥቅል በስጦታ ለመላክ እንዲሁም ከኢትዮ ቴሌኮም ኔትወርክ ውጪ ለመደዋወል አያገለግልም፡፡
    • ስለተቀበሉት ስጦታ የማሳወቂያ መልዕክት በስልክዎ የሚደርስዎ ይሆናል፡፡
    • እስከ ታህሳስ 22 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ ከውጭ አገራት ጥቅል እና አየር ሰዓት በመቀበል 10% በስጦታ ማግኘት ይችላሉ፡፡