በድጋሜ የወጣ የጨረታ ማስታወቂያ SC/L/WRM/004/2015

ኢትዮ ቴሌኮም ለድርጅቱ አገልግሎት የማይሰጡ የተለያዬ ዓይነት ሞዴል ያላቸው አገልግሎት ላይ ያልዋሉ አዳዲስ ኘሪንተሮችን ባሉበት ሁኔታ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ከሰኔ13 ቀን 2ዐ15 ዓ.ም እስከ ሰኔ 28 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ በማንኛውም ጊዜ እና ሰዓት ከ extratenders.com2merkato.com እና afrotender.com ዌብ ሳይቶች በቴሌ ብር አማካኝነት የማይመለስ አንድ መቶ ብር ብቻ በመክፈል በቀላሉ መግዛት ትችላላችሁ፡፡ በተጨማሪም ንብረቶቹን  መመልከት የምትፈልጉ ተጫራቶች የታደሰ መታወቂያችሁን በመያዝ መስቀል ፍላወር በሚገኘው የኢትዬቴሌኮም ማዕከላዊ ዕቃ ግምጃ ቤት በመገኘት ማየት የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን፡፡ ተጨማሪ ማብራርያ ካስፈለገ በስልክ ቁጥሮች +251 114 621 243 እና +251 114 397 022 በመደወል ማግኘት ይቻላል፡፡ ጨረታው ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት አዲስ አበባ አቃቂ በሚገኘው የኩባንያው ዕቃ ግምጃ ቤት ሰኔ 29 ቀን 2015 ዓ.ም ከረፋዱ 5፡00 ሰዓት ላይ ይከፈታል፡፡ ኩባንያው የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

ኢትዮ ቴሌኮም

Share This Post:

Share on facebook
Share on telegram
Share on twitter
Share on linkedin

Follow Us

Recent Posts

Archives