እንደራስ (አነስተኛ ብድር)

የግለሰብ ደንበኞች በቴሌብር እንደሚያከናውኑት የግብይት መጠን እስከ ብር 15,000 ድረስ የአነስተኛ ብድር አገልግሎት

የብድር አይነትየመመለሻ ቀነ ገደብየአገልግሎት ክፍያየተፈቀደው የብድር መጠን ቅጣት
   ዝቅተኛ ከፍተኛ  
ቴሌብር እንደራስ10 ቀናት4%100 ብር4,000 ብር0.5% በቀን
 25 ቀናት9% 10,000 ብር 
 60 ቀናት21% 15, 000 ብር
  •  18 አመት እና ከዛ በላይ
  • አገልግሎት የሚሰጥ የኢትዮ ቴሌኮም ሲምካርድ
  • የቴሌብር እና የኢትዮ ቴሌኮም ንቁ ተጠቃሚ መሆን
  • የኔትወርክ የቆይታ ጊዜ 3 ወር እና ከዛ በላይ
  • የቴሌብር ተጠቃሚ በመሆን ቢያንስ 3 ወር የቆየ
    በማጭበርበር ሪከርድ የተደረጉ ቁጥሮች አገልግሎቱን መጠቀም አይችሉም
  •  የፋይናንሻል አገልግሎት በኢ.ን.ባ የሚለውን ይምረጡ
  •  ከእንደራስ የብድር አማራጮች ውስጥ ይምረጡ
  • መበደር የፈለጉትን የገንዘብ መጠን ይፃፉ
  • መረጃው ትክክል መሆኑን በማረጋገጥ እና የሚስጥር ቁጥር በማስገባት ይጨርሱ
  •  1ን በመጫን የፋይናንስ አገልግሎት የሚለውን ይጫኑ
  • 1ን በመጫን የክሬዲት አገልግሎት የሚለውን ይምረጡ
  • 2ን በመጫን እንደራስን ይምረጡ
    11ን በመጫን ብድር ይውሰዱ የሚለውን ይምረጡ
  •  ከእንደራስ የብድር አማራጮች ውስጥ ይምረጡ
  • መውሰድ የፈለጉትን የገንዘብ መጠኑን ያስገቡ
    የሚጥር ቁጥርዎን በማስገባት ይጨርሱ
ደንብና ግዴታዎችን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ

እንደራስ እና አድራሽ   (አነስተኛ ክሬዲት) አገልግሎትን ለማስጀመር እና ለመጠቀም ደንቦች እና ሁኔታዎች

ዉል  

  1. ይህ ውል (ከዚህ በኋላ "ደንቦች እና ሁኔታዎች" እየተባለ የሚጠራው እንደራስ እና አድራሽ   የክሬዲት አገልግሎት ላይ ተፈጻሚ የሚሆኑ አጠቃላይ ደንብ እና ሁኔታዎች ያካትታል፡፡
  2. እነዚህ ደንቦችና ሁኔታዎች እንዲሁም ከዚህ ጋር የተያያዙ ማሻሻያዎች እና ለውጦች የቴሌብር እንደራስ እና አድራሽ አነስተኛ የብድር አገልግሎት በግለሰብ ደንበኛዉ ተነበው ተቀባይነት ሲያገኙ ("ለማስጀመር" የሚለውን ምርጫ ሲጫን) በደንበኛው ላይ ተፈጻሚ ይሆናሉ፡፡

1.ትርጓሜ

በዚህ የደንቦች እና ሁኔታዎች ውስጥ የተዘረዘሩ ቃላት የሚከተለውን ትርጉም ይይዛሉ፡-

1.1 “የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ" ማለት ቁጥጥር የሚደረግበት የፋይናንስ ተቋም ሲሆን ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በመተባበር ለቴሌብር ደንበኞች እንደራስ እና አድራሽ   አነስተኛ  የክሬዲት  አገልግሎት ለማመቻቸት   የተስማማ የፋይናንስ ተቋም ነው።

1.2 "ኢትዮ ቴሌኮም" የክፍያ መፈጸምያ ሰነድ አዉጭነት ፍቃድ ያለው እና በኢትዮጵያ ንግድ   ባንክ ለሚሰጠዉ እንደራስ  አነስተኛ የብድር አገልግሎት የማመቻቸት ሥራ ለመሥራት  ስምምነት ያለው  ተቋም ነው፡፡

1.3 "የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ" ማለት በአዋጅ ቁጥር 718/2003 (በአዋጅ ቁጥር1282/2015 እንደተሻሻለዉ) መሠረት ለፋይናንስ  ተቋማት ፍቃድ ለመሰጠትና ሥራቸዉን ለመቆጣጠር ሥልጣን ያለዉ ተቋም ነው።

1.4 "ቴሌብር" ማለት ደንበኞች የሞባይል ስልካቸዉን በመጠቀም የፋይናንስ አገልግሎቶችን ለማግኘት የሚያስችል የኢትዮ ቴሌኮም የሞባይል ገንዘብ አገልግሎት የንግድ ስም ነው።

1.5 "የቴሌብር አካውንት" ማለት የቴሌብር ተጠቃሚ ደንበኞች  በኤሌክትሮኒክስ መንገድ ገንዘብ የሚያስቀምጡበት፣ የሚላላኩበት እና የሚቀበሉበት  አካዉንት ነዉ፡፡

1.6 "እንደራስ አነስተኛ የብድር አገልግሎት"  ማለት በኢትዮጵያ ንግድ  ባንክና በኢትዮ ቴሌኮም የጋራ ትብብር ግለሰብ ደንበኞች በኤሌክትሮኒክ ገንዘብ አነስተኛ መጠን ያለው ብድር በቴሌብር ወይም (በUSSD/*127#, Supper App) አማካኝነት የሚያገኙበት የአገልግሎት ዓይነት ነው።

1.7."አድራሽ  የደመወዝ የብድር አገልግሎት"  ማለት  ወርሃዊ    ደመወዛቸው  በቴሌብር  ለሚከፈላቸው የግል እና የመንግስት ተቋማት ሰራተኞች ከየተቋማቸዉ ጋር በሚደረግ ስምምነት  በዚህ ደንብ እና ሁኔታዎች መሰረት በኢትዮ ቴሌኮም የቴሌብር አገልግሎት የኢትዮጵያ ንግድ  ባንክ ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በመተባበር የሚቀርብ  የብድር አገልግሎት ነው፡፡

1.8 “ግለሰብ ደንበኛማለት የተፈጥሮ ሰዉ ሆኖ  በስሙ የቴሌብር አካውንት ያለዉና  በቴሌብር አማካኝነት እንደራስና አድራሽ   አነስተኛ የብድር አገልግሎት ለመዉሰድ የተስማማ  ሰዉ ማለት ነው።

1.9 “ኤሌክትሮኒክ ገንዘብ /- መኒ ከኢትዮጵያ ብር ጋር እኩልመጠን ያለው ገንዘብን   የሚወክል ግለሰብ ደንበኛው የሚያስተዳድረዉ እና በደንበኛዉ የቴሌብር ሂሳብ ዉስጥሚገኝ   የኤሌክትሮኒክስ  የገንዘብ ዋጋ ነው።

1.10 "አንተ" ወይም "የአንተ" ማለት የግለሰብ ደንበኛ ማለት ሲሆን የግለሰቡን የግል ተወካዮችም ያጠቃልላል።

1.11እኛ" "አኛንእና "የእኛማለት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ኢትዮ ቴሌኮም ማለት ነው፡፡

1.12 “የአገልግሎት ክፍያ ” ለእንደራስና አድራሽ አነስተኛ ብድር አገልግሎት በመጀመሪያዉ ቀን በግለሰብ  ደንበኞች የሚፈፀም ክፍያ  ነው::

1.13” ዕለታዊ ክፍያ ማለት ሳይከፈል በቀረዉ የዕዳ መጠን ላይ ግለሰብ ደንበኛዉ በወሰደዉ የብድር ዓይነት መሠረት በየዕለቱ የሚፈፀም የክፍያ ዓይነት ነዉ፡፡

1.14 "የቅጣት ክፍያ" ማለት ግለሰብ ደንበኛዉ በገባዉ ዉል መሠረት የብድሩን ገንዘብ በመክፈያ ቀን ሳይከፍል የቀረ እንደሆን የሚከፍለዉ ገንዘብ ነዉ፡፡

1.15 "የክፍያ ቀን" ማለት ግለሰብ ደንበኛዉ የወሰደዉን ብድር ከፍሎ እንዲያጠናቅቅ የሚጠበቅበት የመጨረሻዉ ቀን ነዉ፡፡

1.16. "የተበላሸ ብድር" ተበዳሪዉ ብድሩን አጠናቆ እንዲከፍል ከሚጠበቅበት የመጨረሻዉ  ዕለት ጀምሮ  ከሚቆጠር 90 ቀናት በኋላ ያልተከፈለ ብድር ማለት ነዉ፡፡

1.17. በአነስታይ ፆታ የተገለፁ ለተባዕታይ ፆታ እንደዚሁም በተባዕታይ ፆታ የተገለፁ ለአነስታይ ፆታ ያገለግላሉ፡፡

1.18. "ግለሰብ" የሚለዉ ቃል ወንድና ሴት ፆታን ለመግለፅ ያገለግላል፡፡

  1. ደንብ እና ሁኔታዎችን ስለመቀበል
    • ይህ አነስተኛ የብድር አገልግሎት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በመተባበር የሚያቀርበዉ ሲሆን ለብድሩ የዋለዉ ገንዘብ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቀረበ ነዉ፡፡
    • እንደራስና አድራሽ አነስተኛ የብድር አገልግሎትን ለማስጀመር ግለሰብ ደንበኛዉ USSD (*127#) ወይም የቴሌብርን መተግበሪያ መጠቀም ይችላል፡፡
    • እንደራስና አድራሽ የብድር አገልግሎትን ለመጠቀም ከማመልከትዎ በፊት እነዚህ ደንብ እና ሁኔታዎች ላይ የተጠቀሰውን የብድሩን አጠቃቀም እና መመሪያ በጥንቃቄ በማንበብ እና በመረዳት መስማማት ይኖርብዎታል፡፡
    • በእነዚህ ደንቦችና ሁኔታዎች ካልተስማሙ እባክዎን ከዝርዝር ምርጫ ውስጥ (“ለማስጀመር” የሚለውን ምርጫ አይጫኑ)
    • ለማስጀመር” የሚለውን አማራጭ ሲጫኑ ደንብ እና ሁኔታዎችን በማንበብ ተረድተው ለማክበር መስማማትዎን ያረጋገጡ ወይም ብድር ክፍያን ለመጠቀም እንደተስማሙ ይወሰዳል።
    • እንደራስና አድራሽ አነሰተኛ የክሬዲት አገልግሎትን በኤሌክትሮኒካዊ መንገድ ብቻ በቴሌብር ለመጠቀም ተስማምተዋል።
    • ደንብ እና ሁኔታዎች ከጊዜ ወደ ጊዜ በኢትዮ ቴሌኮም እና/ወይም በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሊሻሻሉ ወይም ሊለወጡ የሚችሉ ሲሆን ይህንንም ለዉጥ የሚያስገነዝብ ማሳሰቢያ አስቀድሞ  እንዲደርስዎትይደረጋል።  እነዚህ ለዉጦች በቴሌብር  መተግበሪያ ወይም በኢትዮቴሌኮም ድረ ገጽ ላይ ከተለቀቁበት ዕለት ጀምሮ ተግባራዊ ይደረጋሉ፡፡
    • ደንብና ሁኔታዎች በኤሌክትሮኒክስ መንገድ ተቀባይነት ካገኘበት ጊዜ ጀምሮ በእርስዎ እና በእኛ መካከል በህጋዊ መንገድ አስገዳጅ ውል ይሆናል።በዚህ ስምምነት ስር ያለዎትን ማንኛውንም መብት ወይም ግዴታ ለሌላ ለማንም ማስተላለፍ አይፈቀድልዎትም።
    • ግለሰብ ደንበኛው ገንዘቡን ለህጋዊ ዓላማ ብቻ ለማዋል ተስምቷል።
  1. የእንደራስ ብድር አገልግሎትን ለማስጀመር

የብድር አገልግሎትን ከኢትዮ ቴሌኮም እና ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር ለማስጀመር ቢያንስ፡-

  • እነዚህን ደንቦችና ሁኔታዎችን ሊያነቡ፣ሊረዱ እና ሊስማሙ ይገባል፣
  • 18 ዓመት እና ከዚያ በላይ መሆን፣
  • አገልግሎት የሚሰጥ የኢትዮ ቴሌኮም ሲም ካርድ መያዝ፣
  • የቴሌብር እና የኢትዮ ቴሌኮም አገልግሎቶችን እንደ ዳታ/ድምጽ/አጭር የጽሁፍ መልዕክት የሚጠቀሙ መሆን አለብዎት፡፡
  • የቴሌብር እና የቴሌኮም የደንበኝነት ቆይታ 3 ወር እና ከዛ በላይ መሆን አለበት፡፡
  1. አድራሽ አነሰተኛ ብድር ለማግኘት መሰረታዊ መስፈርቶች፤
    • የግለሰብ ደንበኛው የመበደር አቅም፣ ደንበኛው የብድር ክፍያ አገልግሎት ለመጠቀም ጥያቄ ካቀረበበት ቀን በፊት ባደረገው የ6 ወር የቴሌብር የገንዘብ እንቅስቃሴ፣ቀደም ሲል የወሰደዉን ብድር የመክፈል ታሪክ እና በቴሌኮም አገልግሎት አጠቃቀም ይወሰናል። ከታች ያሉት የቴሌብር ግብይቶች የደንበኛ የብድር አቅምን ለማስላት ይውላሉ።
  • የአየር ሰዓት መሙላት ወይም ጥቅል መግዛት (በራስ አገዝ ወይመ ከወኪሎች)፣
  • ዕቃ ወይም አገልግሎት በመግዛት ግብይት መፈጸም፣
  • ቢል ክፍያ (በራስ አገዝ ወይም ከወኪሎች)፣
  • ለእርስዎ ወይም የሌላ ደንበኛ የፍጆታ አገልግሎት ክፍያ መፈፀም (በራስ አገዝ ወይም ከወኪሎች)፣
  • በልክ ዲስፐርስመንት ( የቀን ሠራተኞች ክፍያ ፣ደመወዝ ፣ዕርዳታ፣ጡረታ፣…) ክፍያ በቴሌብር መቀበል፣
  • ከውጭ አገር ገንዘብ መቀበል፣
  • የትኬት ግዢ፣
  • ለገንዘብ ማሰባሰቢያ የእርዳታ ክፍያ( ፈንድ ረይዚንግ)፣
  • በቴሌብር ወኪሎች በኩል ገንዘብ መቀበልና ወጪ ማድረግ፣
  • የቁጠባ አገልግሎት፣
  • ገንዘብ መላክ፣
  • የቴሌኮም ፍጆታ (ድምጽ፣ ዳታ ወይም መልዕክት)፣
  • በቴሌብር የተወሰደን ብድር በአግባቡ የመክፈል የቀደመ ታሪክ ፡፡
  • ብቁ ለመሆን ደንበኞች ከቴሌኮም አገልግሎት ፍጆታ በተጨማሪ የቴሌብር አገልግሎት መጠቀም አለባቸው፡፡
    • አድራሽ ብድር ለማግኘት ወርሃዊ ደመወዝን በቴሌብር አማካኝነት መቀበል እና ከሚሰሩበት ተቋም ጋር የሚደረግ  ስምምነት በቂ ነዉ፡፡
  1. የብድሩ መጠን እና ክፍያ
    • የግቢይት መጠንዎን መሠረት በማድረግ በሚፈቀደው ዝቅተኛ እና ከፍተኛ የክሬዲት  መጠን መካከል ማንኛውንም መጠን መበደር ይችላሉ፡፡
    • በሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 576/2018 መሠረት ለኢትዮጵያ የአደጋ ስጋት ምላሽ ፈንድ ከጠየቁት ጠቅላላ የብድር መጠን ላይ አንድ በመቶ (1%) ተቀናሽ ተደርጎ ቀሪዉ ወደ ቴሌብር አካውንትዎ ገቢ ይደረጋል፡፡
    • ሌላ ብድር ለማግኘት መጀመሪያ ከቴሌብር የወሰዱትን ብድር መክፈል ይጠበቅብዎታል፡፡
    • ያለብዎትን ብድር በከፊል ወይም በሙሉ በአንድ ጊዜ መክፈል ይችላሉ፡፡
    • የክሬዲት ክፍያ ቀን ብድሩን ከወሰዱበት ቀን ጀምሮ በሚቆጠር እንደ ብድሩ ዓይነት 10 ቀን፣25ቀን እና 60 ቀናት ውስጥ ይሆናል።
    • ለ10 ቀናት ክሬዲት ከፍተኛዉ  የክሬዲት ገደብ ብር 4,000 ብር፣ ለ25-ቀናት ክሬዲት ከፍተኛዉ  የክሬዲት ገደብ  ብር 10,000  እና ለ 60 ቀናት የክሬዲት ገደብ ከፍተኛዉ  የክሬዲት ገደብ  ብር 15,000  ሲሆን ለሁሉም ክሬዲት ዓይነቶች ዝቅተኛዉ የክሬዲት መጠን 100.00 ( መቶ ብር ብቻ ) ነዉ፡፡
    • የ10 ቀን ክሬዲትዎን በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ከከፈሉ፣በመጀመሪያ ቀን የአገልግሎት ክፍያ 1.25% የሚከፍሉ ሲሆን በቀሪው የመክፈያ ጊዜዎ የክሬዲት ገደብ ላይ በመመስረት የዕለታዊ  ክፍያ ከ0.50% እስከ 0.80% ይከፍላሉ።
    • የ25 ቀን ክሬዲትዎን በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ከከፈሉ፤በመጀመሪያ ቀን የአገልግሎት ክፍያ 2.50% የሚከፍሉ ሲሆን በቀሪው የመክፈያ ጊዜዎ የክሬዲት ገደብ ላይ በመመስረት  ዕለታዊ  ክፍያ ከ0.50% እስከ  80% ይከፍላሉ።
    • የ60 ቀን ክሬዲትዎን በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ከከፈሉ ፤በመጀመሪያ ቀን የአገልግሎት ክፍያ 6.50% የሚከፍሉ ሲሆን በቀሪው የመክፈያ ጊዜዎ የክሬዲት ገደብ ላይ በመመስረት  ዕለታዊ ክፍያ ከ0.50% እስከ 0.80% ይከፍላሉ።
    • የ4 ወራት ደመወዝ የአድራሽ ክሬዲት የ12 ወራት የመክፈያ ጊዜ እና የ21% የአገልግሉት ክፍያ አለው፡፡
    • የ3 ወራት ደመወዝ የአድራሽ ክሬዲት የ9 ወራት የመክፈያ ጊዜ እና የ18% የአገልግሉት ክፍያ አለው፡፡
    • የ2 ወራት ደመወዝ የአድራሽ ክሬዲት የ6 ወራት የመክፈያ ጊዜ እና የ15% የአገልግሉት ክፍያ አለው፡፡
    • ለአንድ ወር ደመወዝ አድራሽ የአገልግሎት ክፍያ 14% ሲሆን የመክፈያ ጊዜ 4 ወር ይሆናል።
    • ለአንድ ወር ደመወዝ አድራሽ የአገልግሎት ክፍያ 10% ሲሆን የመክፈያ ጊዜ 3 ወር ይሆናል።
    • ለግማሽ ወር ደመወዝ አድራሽ የአገልግሎት ክፍያ 8% ሲሆን የመክፈያ ጊዜ 2 ወር ይሆናል።
    • የደመወዝዎ 25% አድራሽ የአገልግሎት ክፍያ 4% ሲሆን የመክፈያ ጊዜ 1 ወር ይሆናል።
    • ለአድራሽ    የብድር  ክፍያዉ  በወሰዱት  የብድር ጊዜ ተከፋፍሎ በየወሩ  ይከፈላል ፡፡
    • ያለብዎትን ብድር በክፍያ ቀን ውስጥ የማይከፍሉ ከሆነ ተጨማሪ የቅጣት ክፍያ 0.17% በየዕለቱ ይከፍላሉ፡፡
    • በጉርሻ የሚያገኙት ገንዘብ ለክሬዲት ክፍያ አይውልም፡፡
  1. ያልተፈፀመ ክፍያ አሰባሰብ
    • የሚጠበቅብዎትን ክሬዲት ክፍያ በሰዓቱ ካልፈፀሙ ኢትዮ ቴሌኮም እና / ወይም የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የቀረውን የብድር መጠን ከቴሌብር ሂሳብዎ ወይም ከቁጠባ አካውንቶ ወዲያውኑ ተቀናሽ ያደርጋሉ፡፡
    • ብድሩ መከፈል ባለበት ጊዜ ሳይከፈል የቀረ እንደሆነ ኢትዮ ቴሌኮም እና/ወይም የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ ከባለዕዳዉ የኢትዮጵያ ንግድ  ባንክ ወይም ሌሎች ባንኮች ሒሳብ በቀጥታ መቁረጥን ጨምሮ ማናቸዉም አማራጭ ዜዴዎች በመጠቀም ከፍርድ ቤት ዉጭ ባለ አማራጭ ዕዳዉን መሰብሰብ ይችላሉ፡፡
    • ከፍርድቤት ዉጭ ባለ  አማራጭ  ዕዳዉን  ለመሰብሰብ   ያግዝ  ዘንድ ኢትዮ ቴሌኮም እና/ወይም የኢትዮጵያ ንግድ  ባንክ የግለሰብ ደንበኛዉን  አድራሻ ማናቸዉም አማራጭ ዘዴዎች በመጠቀም አፈላልገዉ በማግኘት  ዕዳዉን የመሰብሰብ መብት ያላቸዉ መሆኑን ግለሰብ ደንበኛዉ ተስማምቷል፡፡
    • ዕዳዉመከፈል ባለበት ጊዜ ሳይከፍል የቀረ እንደሆነ ኢትዮ ቴሌኮም እና/ወይም የኢትዮጵያ ንግድ  ባንክ የግለሰብ ደንበኛዉን አድራሻ እና ሌሎች ለእዳው አሰባሰብ አስፈላጊ የሆኑ መረጃዎችን በመሰብሰብ ሥራ ላይ ለሚሳተፍ ሦስተኛ ወገን (ድርጅት ወይም ግለሰብ) አሳልፈዉ መስጠት  የሚችሉ  መሆኑን ግለሰብ ደንበኛዉ ተስማምቷል፡፡
    • ከፍርድ ቤት ዉጭ ባለ አማራጭ ዕዳዉ የማይከፈል ከሆነ ኢትዮ ቴሌኮም እና/ወይም የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጉዳዩን ወደ መደበኛ ፍርድ ቤት በራሳቸዉ ወይም በሌላ የሕግ አገልግሎት ሰጪ ተቋም ወይም በግለሰብ ጠበቃ አማካኝነት የመውሰድና የመክሰስ ሙሉ መብት አላቸው፡፡
    • የተበላሸ ብድር ውስጥ ያለ ደንበኛ አጠቃላይ ዕዳውን ለመክፈል "የተበላሸ ብድርን በተራዘመ የመክፈያ ጌዜ አማራጭን" መጠቀም ይችላል። እንደ ተበላሸው የብድር መጠን ከ0.75%-1% የአገልግሎት ክፍያ ይኖረዋል፡፡
    • የብድር ማራዘሚያ ጥያቄ ማቅረብ የሚቻለው ብድሩ የሚከፈልበት ቀን ከመድረሱ በፊት ነው። ብድሩን ማራዘም የሚቻለው ቢበዛ ለ10 ቀናት ብቻ ሲሆን፣ ለማራዘሚያውም በቀን 0.08% የአገልግሎት ክፍያ ይታሰባል።

7.ተፈጻሚነት ያለው ሕግ

የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕጎች፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ መመሪያዎች፣ እንዲሁም የኢትዮጵያ ንግድ ባንክና የኢትዮ ቴሌኮም አግባብነት ያላቸው የአሠራር ሥርዓቶች በእነዚህ ደንብ እና ሁኔታዎች ላይ ተፈጻሚ ይሆናሉ፡፡

  1. መረጃ ስለመጠየቅ

ስለ    እንደራስ  እና  አድራሽ አገልግሎት፣ ሂደት፣ ደንብ  እና  ሁኔታዎች ጋር   ለተያያዘ  ማንኛውም   ጥያቄ    በቴሌብር የደንበኞች  ግንኙነት  ማእከል (127 በመደወል), ወደ 126 አጭር የጽሁፍመልዕክት    በመላክ፣ በሶሻል ሚዲያ (https://telehub.ethiotelecom.et/) ተጨማሪ  መረጃ ማግኘት  ይችላሉ።

  1. የውል መቋረጥ

ማንኛውንም የአነስተኛ ቁጠባ እና ብድር አገልግሎቶችን ያለቅድመ ማስጠንቀቂያ ወይም ያለማስታወቂያ በእርስዎ  አላግባብ  መጠቀም ምክንያት ሙሉ  በሙሉ  ወይም በከፊል  ለማገድ ወይም ለማቋረጥ መብት ይኖረናል። የዚህ ውል መቋረጥ ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የሁለቱንም ተዋዋይ ወገኖች መብቶችን እና ግዴታዎችን ሊነካ አይችልም።

  1. ቅሬታእና የግጭት አፈታት

  ቅሬታዎች በአካል፣ በጽሁፍ፣ በፖስታ፣ በፋክስ፣ በኢሜል ወይም በስልክ ሊቀርቡ ይችላሉ፡፡ኢትዮ ቴሌኮም  ቅሬታዎን በተገቢው ጊዜ ለመፍታት ሁሉንም እርምጃዎች ይወስዳል። በመልሱ  ካልረኩ ጉዳዩን  ወደ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በቅደም ተከተል  መውሰድ ይችላሉ፡፡ቅሬታዉ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ኢትዮ ቴሌኮም ከቀረበበት ጊዜ ጀምሮ በሚቆጠር ሰላሳ ተከታታ ይቀናት ዉስጥ ተዋዋይ ወገኖች  ስምምነት ላይ መድረስ ካልቻሉ  ጉዳዮቻቸውን በኢትዮጵያ ስልጣን ላለው ፍርድ ቤት ብቻ ለማቅረብ ተስማምተዋል።

  1. የመያዝ መብት

እኛ ጋር ያለብወትን እዳ ካልከፈሉ በተለይም በጥሬ ገንዘብ፣ዕቃዎች፣ዋስትናዎች፣ውድ ጌጦች፣ቼኮች እና ማንኛውን ተንቀሳቃሽም ሆነ የማይነቀሳቀስ ንብረትዎ ላይ አጠቃላይ የመያዝ መብት ይኖረናል፡፡እኛ ጋር ያለብዎትን እዳ የማይከፍሉ ከሆነ እና የማቻቻል መብት ሲፈጠር በመያዣ መብት ስር የተያዙ ንብረቶችን ላልተከፈለው ብድር እንደ ዋስትና ተደርጎ መቁጠር ይቻላል፡፡

  1. ዕዳ ስለማቻቻል

የወሰዱትን አነስተኛ  ብድር  መጠን እንዲከፍሉ ካሳወቅን በኋላ በተቀመጠለት ጊዜ ገደብ ውስጥ መመለስ  ካልቻሉ ባንክ ውስጥ ካሉዎት ሌሎች የባንክ ተቀማጭ ጥሬ ገንዘብ፣ ቁጠባ፣ተርም ዲፖዚት፣የጋራ ወይም የተናጠል ከሆኑት ላይ ያለብዎትን  ዕዳ መጠን ያህል  ያለምንም ቅድመ ሁኔታ መዉሰድ እንድንችል ተስማምተዋል፡፡

  1. ማስተባበል

የቴሌብር  ሚስጥር  ቁጥር (ፒን)  በሚስጥር  መቀመጥ  አለበት ከእርስዎ ሌላ ለማንም ተደራሽ መሆን የለበትም። የሚስጥር   ቁጥርዎን  ሌላ  ሶስተኛ  ወገን  እንዲያዉቀዉ በማድረግዎ  ወይም  በየጊዜው    ባለመቀየርዎ፣ ያልተፈቀደ   የቴሌብር   አጠቃቀም በማከናወንዎ፣ የሞባይል ስልክዎ ወይም ሲም  ካርድ  ሲሰረቅብዎ   ወይም ሲጠፋብዎ ለሚመለከተዉ  አካል  ፈጥነዉ ባለማሳቅዎ እና ባለማስዘጋትዎ  የሚደርስብዎ  ኪሳራ /ጉዳት የእርስዎ ኃላፊነት ብቻ ይሆናል፡፡