ስለ ኢትዮ ቴሌኮም


አጭር ታሪካዊ ዳራ
የቴሌኮሙኒኬሽን አገልግሎት በኢትዮጵያ የተጀመረው በዳግማዊ ሚኒሊክ ዘመነ መንግሥት በ1886 ዓ.ም. ከሐረር ከተማ ወደ ሐገሪቷ ርዕሰ መዲና አዲስ አበባ በተዘረጋው የቴሌፎን እና ቴሌግራፍ መስመር አማካኝነት ነበር፡፡ ከዚያም በኋላ የስልክ መገናኛ መስመሮች ከዋና ከተማዋ አዲስ አበባ በሁሉም አቅጣጫዎች እየተስፋፉ በመሄዳቸው በርካታ የአገሪቷ ዋና ዋና ከተሞች በኦፕሬተሮች አማካይነት የቴሌኮሙኒኬሽን አገልግሎት ተጠቃሚ ለመሆን በቅተዋል፡፡

የኢትዮ ቴሌኮም አመሠራረት
የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፑብሊክ መንግሥት ከ1998-2002 ዓ.ም. የተነደፈውን የአምስት ዓመት እቅድ በማስቀጠል እንዲሁም ጥረቱን በትምህርት፣ በጤናና በግብርና ላይ ትኩረት ከመስጠት ባሻገር የቴሌኮሙኒኬሽን አገልግሎት ለሀገራችን ሁለንተናዊ ልማት ወሳኝ ኃይል መሆኑን በመገንዘብና አገልግሎቱን ለማሻሻል በመወሰን የሀገራችንን ቀጣይ እድገት ለማገዝ ካለው ፍላጎት አኳያ ኢትዮ ቴሌኮም ሕዳር 21 ቀን 2003 ዓ.ም በአዲስ ስያሜና በአዲስ መልክ እንዲመሠረት ተደርጓል፡፡

መዋቅራዊ አደረጃጀት (በተለያዩ ጊዚያት ከተሰጡ አዳዲስ ስያሜዎች ጋር)
- 1886 ዓ.ም፡- የኢትዮጵያ የቴሌፎንና የቴሌግራፍ ማዕከላዊ አስተዳደር
- 1900 ዓ.ም፡- የኢትዮጵያ የፖስታ፣ ቴሌግራፍ እና ቴሌፎን ማዕከላዊ ቢሮ
- 1903 ዓ.ም፡- የፖስታ፣ የቴሌግራፍ እና ቴሌፎን ሚኒስቴር (ፖቴቴ)
- 1945 ዓ.ም፡- የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት ቴሌኮሙኒኬሽን ቦርድ
(የድርጅቱን የተለያዩ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊነት የሥራ መደቦች በወጣት ኢትዮጵያዊያን የመተካት መርሐ ግብር በ1960 ዓ.ም ተከናውኖ ተጠናቀቀ) ፤በተለያዩ ጊዚያት የተሰጡ አዳዲስ ስያሜዎችም የሚከተሉት ናቸው፡-
- 1967 ዓ.ም:- የሶሻሊስት ኢትዮጵያ ጊዜያዊ ወታደራዊ መንግሥት የቴሌኮሙኒኬሽን አገልግሎት ድርጅት
- 1989 ዓ.ም:- የኢትጵያ ቴሌኮሙኒኬሽን ኮርፖሬሽን
- 2003 ዓ.ም:- ኢትዮ ቴሌኮም
ወደ ኢትዮ ቴሌኮም ሽግግር
የፌደራል መንግስት የቴሌኮም አገልግሎቶችን ለአገራዊ ልማት ቁልፍ ወስዶ በትኩረት እንዲሰራ መወሰኑን ተከትሎ ኢትዮ ቴሌኮም ከህዳር 29 ቀን 2010 ዓ.ም ጀምሮ አሁን ያለበትን ደረጃ አግኝቷል። በዚህም የሀገሪቱን የቴሌኮም መሠረተ ልማትና አገልግሎቶች ወደ ዓለም አቀፍ ደረጃ በመቀየር በዘርፉ መሻሻል ላይ ትልቅ ለውጥ በማድረግ የሀገሪቱን ልማት ለማሳለጥ ተችሏል።
የቴክኖሎጂ ዕድገት
ኤል.ቲ.ኢ አድቫንስድ አገልግሎት
ከፍተኛ ፍጥነት ያለው የ4ጂ ኤል.ቲ.ኢ አድቫንስድ ሞባይል ኢንተርኔት አገልግሎት በ2012 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ በተመረጡ ቦታዎች አገልግሎት መስጠት ጀመረ
2020የምድር ሳተላይት ጣቢያ
- በሱሉልታ የምድርሳተላይት ጣቢያ አማካኝነት ዓለምአቀፍግንኙነትተጀመረ
በሦስት የተለያዩ አቅጣጫዎች የተተከሉ ጣቢያዎች
- በ1971 ዓ.ም: - ትልቁና 32 ሜትር ሬዲየስ ስፋት ዲሽ ያለው የሱሉልታ የምድር ሳተላይት መገናኛ አውታር ተቋቁሞ አገልግሎት መስጠት ጀመረ
- በ1980 ዓ.ም: - ሁለተኛውና 13 ሜትር ሬዲየስ ስፋት ዲሽ ያለው የሱሉልታ የምድር ሳተላይት መገናኛ አውታር ተቋቁሞ አገልግሎት መስጠት ጀመረ
- በ1993 ዓ.ም: - ሦስተኛውና 3 ሜትር ሬዲየስ ስፋት ዲሽ ያለው የሱሉልታ ባለዲጂታል የምድር ሳተላይት መገናኛ አውታር ተቋቁሞ አገልግሎት መስጠት ጀመረ::
የዓለም አቀፍ እና አገር ውስጥ የሬዲዮ ጣቢያ አገልግሎቶች
ለዓለም አቀፍ እና አገር ውስጥ መገናኛ አገልግሎቶች የሚውሉ የሬዲዮ ጣቢያዎች በ1944 ዓ.ም እንዲቋቋሙ ተደርጎ አገልግሎት መስጠት ጀመሩ::
1952- በዘመናዊየቴሌኮምአገልግሎት አማካኝነት ኢትዮጵያን ማገናኘት
- የሀገራችንንልማትየሚያጎለብቱናከፍተኛየደንበኛእርካታን ሊያረጋግጡ የሚችሉከፍተኛጥራትናተመጣጣኝ ዋጋ ያላቸውአዳዲስየቴሌኮምምርቶችንእናአገልግሎቶችን ማቅረብ
- በደንበኞች ዘንድ በቀላሉ ሊታወቅ የሚችል ታዋቂና ዝነኛ የኩባንያ ብራንድ መገንባት
- ኢትዮቴሌኮምዓለምአቀፍ ደረጃውን የጠበቀ ሥራ ለማከናወን የሚያስችል የአመራር ብቃትና የሰው ኃይል አቅም እና ተሰጥኦ መገንባት
- የማህበረሰባዊና የአካባቢልማትን መደገፍ
ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ የቴሌኮም አገልግሎት ሰጪ ተቋም ሆኖ ማየት::
ደንበኛን ማስቀደም፡– የደንበኞችንና የሠራተኞችን ፍላጎትና እሴት በማክበር ፈጣን ምላሽ መስጠት፤
ልቆ መገኘት፡– ለደንበኞቻችን የላቀ አገልግሎት ለመስጠት ዘወትር ለጥራት፣ ለቅልጥፍና እና ለውጤታማነት በቁርጠኝነት መሥራት፤
ተጠያቂነት:– ሁሉንም ተግባሮቻችን በሀቀኝነት፣ በግልፀኝነት እና በታማኝነት በማከናወን ኃላፊነታችንን መወጣት፤
አለማዳላት፡– ሁሉንም ደንበኞቻችን ያለምንም አድልዎ በእኩልነት ማገልገል፤
መጋራት፡– የተቋማችንን ተልዕኮ ለማሳካት በየዕለቱ በጋራ በመንቀሳቀስና በመደጋገፍ ተቀናጅተን ለውጤት መትጋት፡፡