ይህ ሪፖርት ከሐምሌ 2011 እስከ ሰኔ 2012 ያለውን የኢትዮ ቴሌኮም የአንድ ዓመት የሥራ አፈጻጸም የሚገልጽ ነው፡፡

ኢትዮ ቴሌኮም በበጀት ዓመቱ መጀመሪያ ላይ ለህዝብ ይፋ ያደረገውን የሦስት ዓመት ስትራቴጂና የ2012 በጀት ዓመት እቅድ ተግባራዊ በማድረግ ተቋሙን በደንበኞቹና በአጋሮቹ ዘንድ ተመራጭ ለማድረግ ሰፊ ሥራዎችን ሲያከናውን ቆይቷል፡፡

በበጀት ዓመቱ የተያዙ ስትራቴጂያዊ ግቦችን ለማሳካት መጠነ ሰፊ የለውጥና የማሻሻያ ሥራዎች የተከናወኑ ሲሆን በዋናነትም የደንበኞች ተሞክሮን ማሻሻልና እርካታን ማሳደግን ታሳቢ ያደረገ የኦፕሬሽን ልህቀት ማምጣት፣ የአገልግሎት ተደራሽነትና ጥራትን ማሳደግ፣ የደንበኞችን አቅም ያገናዘበ የታሪፍ ማሻሻያ ማድረግ፣ የሀብት አጠቃቀም ማሻሻልና የፋይናንስ አቅምን ማጎልበት፣ የገጽታ ግንባታ ሥራዎችን ማከናወን፣ የተቋማችን ሠራተኛና አመራር ስትራቴጂን የመንደፍ፣ የማስፈጸምና የመፈጸም እንዲሁም ውሳኔ የመስጠት አቅምን ማጎልበት የሚያስችሉ በርካታ ሥራዎች ተከናውነዋል፡፡

በበጀት ዓመቱ ኩባንያችን 47.7 ቢሊዮን ብር አጠቃላይ ገቢ በማግኘት የእቅዱን 105.1% በማሳካት የላቀ አፈጻጸም አስመዝግቧል፤ ይህ ውጤት ከባለፈው በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር በ31.4% አድጓል፡፡ ይህን ከፍተኛ እና ከእቅድ በላይ የሆነ ገቢ ማግኘት የተቻለው የደንበኞች የቴሌኮም አጠቃቀምን ለማሳደግና ተሞክሯቸውን ለማሻሻል የሚስችሉ የኔትወርክ ማስፋፊያና የአገልግሎት ጥራትን ለመጨመር የሚያስችሉ ማሻሻያዎችን በመተግበር፣ የ4ጂ አገልግሎትን በመላው አዲስ አበባ እና ከፍተኛ ፍጥነት ያለው የ4ጂ አድቫንስድን በተወሰኑ አካባቢዎች በመዘርጋት፣ የባለገመድ ብሮድባንድ አገልግሎት ላይ ሰፊ ማሻሻያዎችና እጅግ ከፍተኛ የዋጋ ቅናሽ በማድረግ እንዲሁም ከመደበኛ የቴሌኮም አገልግሎቶች በተጨማሪ ሌሎች እሴት የሚጨምሩ 16 አዳዲስ እና 25 ነባር የሀገር ውስጥና የዓለም አቀፍ ምርትና አገልግሎቶችን በማሻሻል ለደንበኞች በማቅረብ ነው፡፡

የውጭ ምንዛሪ ከሚያስገኙ አገልግሎቶች 147.7 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር የተገኘ ሲሆን ይህም የእቅዱን 107% በማሳካት የላቀ አፈጻጸም ያስመዘገበ ሲሆን ካለፈው በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ50% እድገት አስመዝግቧል፡፡ በውጭ ምንዛሪ የሚገኘውን ገቢ ለማሳደግ የቴሌኮም ማጭበርበርን በተለያዩ ስልቶች በመከላከል እና የተቋም ደህንነትን ከማረጋገጥ አኳያ ልዩ ትኩረት ማድረግ እንዲሁም ከዓለም አቀፍ ቢዝነስ አጋሮቻችን ጋር ያለውን ግኑኝነት ለማሻሻልና ለማጠናከር ሰፊ ሥራዎች በመከናወናቸው ነው፡፡ ገበያው በሚጠይቀው መሠረት አዳዲስ አሰራሮችን መከተል፣የተገኘው ገቢ በአገልግሎት አይነት ሲታይ የሞባይል ድምጽ ገቢ ድርሻ 49%፣ የዳታና ኢንተርኔት ገቢ ድርሻ 29%፣ የዓለም አቀፍ ንግድ ገቢ ድርሻ 9%፣ እሴት ከሚጨምሩ አገልግሎቶች (VAS) 9.4% እንዲሁም ከሌሎች አገልግሎቶች የተገኘው ገቢ ድርሻ 3.6% ይይዛል፡፡

በበጀት ዓመቱ ከተከናወኑ ዋና ዋና ክፍያዎች መካከል 11.3 ቢሊዮን ብር ታክስ እና 4 ቢሊዮን ብር ዲቪደንድ ለመንግስት የተከፈለ ሲሆን በቬንደር ፋይናንሲንግ ሞዳሊቲ ለተከናወኑ ፕሮጀክቶች ብድር 10.2 ቢሊዮን ብር ወይም 318.4 ሚሊዮን ዶላር ክፍያ የተፈጸመ ሲሆን እነዚህንና ሌሎች ክፍያዎችን ፈጽሞ ወደ ቀጣዩ በጀት ዓመት በጥሩ የጥሬ ገንዘብ መጠን (Cash Position) ተሸጋግሯል፡፡

በበጀት ዓመቱ አጠቃላይ የደንበኞቻችን ብዛት 46.2 ሚሊዮን የደረሰ ሲሆን ካለፈው በጀት ዓመት ማጠናቀቂያ ሲነጻጸር የ5.8% እድገት አሳይቷል፡፡ በአገልግሎት አይነት ሲታይ የሞባይል ድምፅ ደንበኞች 44.5 ሚሊዮን፣ የዳታzs እና የኢንተርኔት ተጠቃሚ 23.8 ሚሊዮን፣ የመደበኛ ብሮድባንድ (Fixed Broadband) ደንበኛ 212.2 ሺህ እንዲሁም መደበኛ ስልክ 980 ሺህ ደንበኞች ናቸው፡፡ በበጀት ዓመቱ በባለገመድ ብሮድባንድ አገልግሎት ላይ በተደረጉ የአገልግሎት ማሻሻያዎችና ከፍተኛ የታሪፍ ቅናሽ ምክንያት የብሮድባንድ ደንበኞች ቁጥር በ135% ማሳደግ ተችሏል፡፡ በዚህም አጠቃላይ የቴሌኮም ስርጸት (teledensity) 46.1% ደርሷል፡፡

ኩባንያችን 16,506 ቋሚ እና 19,959 የኮንትራት ሠራተኞች ያሉት ሲሆን የተቋሙን ቀጣይነት ያለው እድገት ለማረጋገጥ የሰው ኃይሉን በእውቀት፣ በክህሎትና በመልካም የሥራ ባህል ከማነጽ አኳያ የተለያዩ የሥልጠና ፕሮግራሞችን በመቅረጽ 10,665 ሠራተኞች ስልጠና እንዲወስዱ ተደርጓል፡፡ በተጨማሪም የሠራተኛውን ተነሳሽትና የባለቤትነት መንፈስ የሚያሳድጉ ሥራዎች የተከናወኑ ሲሆን ለአብነት ያህል ሠራተኞችን በተቋሙ ስትራቴጂ ዝግጅትና የሥራ አፈጻጸም ግምገማ ላይ ተሳትፎ እንዲኖራቸውና ግብዓት እንዲሰጡ የማድረግ፣ የሥራ መገልገያ መሣሪያዎችን አቅርቦት ማሻሻል፣ የሥራ ከባቢን አመቺና ደህነንቱን የማረጋገጥ፣ የተለያዩ የማበረታቻ ሥርዓቶችን በመተግበር እንዲሁም በሁሉም የተቋሙ የሥራ ቦታዎች የሠራተኞች ቀን በማክበር የተሻለ የሥራ ከባቢን የሚፈጥሩ ሥራዎች ተከናውነዋል፡፡ በተጨማሪም የኢትዮ ቴሌኮም ምርትና አገልግሎት ለደንበኞች የሚያደርሱ 249 ሺህ አጋሮች ያሉ ሲሆን በአጠቃላይ ከቴሌኮም ጋር ተዛማጅ በሆኑ ሥራዎች ተሰማርተው የሥራና የገቢ እድል የተፈጠረላቸው ዜጎች ቁጥር ከ287 ሺህ በላይ ደርሰዋል፡፡

ኩባንያችን ለደንበኞቹ ከሚሰጠው የቴሌኮም አገልግሎት በተጨማሪ ለማህበረሰባችን ፋይዳ ባላቸው ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በስፋት በመሳተፍ ማህበራዊ ኃላፊነቱን በተቀናጀ መልኩ በሚገባ ተወጥቷል፡፡ በበጀት ዓመቱ በአይነት፣ በአገልግሎትና በገንዘብ በድምሩ 1.15 ቢሊዮን ብር በላይ አስተዋጽዖ አድርጓል፡፡ በመላው ሃገሪቱ በትምህርት፣ በጤና፣ በአካባቢ ጥበቃ፣ አረንጓዴ ልማትና ማስዋብ ላይ ተሳትፏል፡፡ ኩባንያችን ከሚያደርገው እገዛ በተጨማሪ ሠራተኞቻችን በበጎ ፍቃደኝነት ላይ የተመሠረተ አስተዋፅኦ በማድረግ በአጠቃላይ የኢኮኖሚ ችግር ያለባቸውን የህብረተሰብ ክፍሎች ከ2.1 ሚሊዮን ብር የገንዘብ እና የተለያዩ የቁሳቁስ ድጋፍ እንዲሁም ደም በመለገስና የመልካም ፍቃድ አገልግሎት በመስጠት እጅግ የሚበረታታና አርአያነት ያለው ተግባር አከናውነዋል፡፡

ኩባንያችን በዓለም አቀፍ ደረጃ የሰው ልጆችንና ተቋማትን እየተፈታተነ ያለው የኮቪድ-19 ወረርሽኝ የሚያስከትለውን ተጽዕኖ ለመቋቋም የተለያዩ እርምጃዎች የወሰደ ሲሆን የቴሌኮም አገልግሎት ለድርጅቶች፣ ለመንግስትና ለማህበረሰቡ እንደዋነኛ የመገናኛና የሥራ ማስኬጃ አማራጭ በመሆኑ አብዛኛው ማህበረሰብ በቴሌኮም አገልግሎት ላይ በመመርኮዝ ከቤቱ ሆኖ ሥራውን ማከናወን፣ ማህበረሰባችን ማህበራዊ ርቀትን ጠብቆ የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴውን ማከናወን እንዲችል ለማገዝ ከፍተኛ ቅናሽ ያለው ፓኬጅ ለተጠቃሚዎች ቀርቧል፡፡

በተጨማሪም የኮቪድ-19 ወረርሽኝን ለመከላከል ከፍተኛ ሀብት በመመደብና ትኩረት በመስጠት የጎላ ሚና የተጫወተ ሲሆን የአንድ መቶ ሚሊዮን ብር (100 ሚሊዮን ብር) የገንዘብ ድጋፍ ከማድረግ አንስቶ፣ የማህበረሰቡን ግንዛቤ ለማሳደግ የስልክ ጥሪን የኮቪድ-19 መከላከል መልዕክቶች ለማስተላለፍ መጠቀም፣ ማህበረሰቡ ኮቪድን ለመከላከልና መረጃና አስፈላጊ እርዳታ ለማግኘት የሚችልባቸው አጫጭር ቁጥሮች ለፌዴራልና ለክልል መንግስታት በነጻ የማቅረብ፣ የጤና ሚኒስቴርና የማህበረሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ወረረሽኙን አስመልክቶ በድረ ገጻቸው የሚስተላልፉትን መረጃ በነጻ ማድረስ፣ በሀገር ውስጥና በውጭ ያሉ ኢትዮጵያዊያንና የኢትዮጵያ ወዳጆች በኮቪድ ምክንያት እርዳታ ለሚያስፈልጋቸው አካላት የሚሆን የገንዘብ ማሰባሰቢያ አማራጮችን የማቅረብ፣ በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር አማካይነት በኮቪድ – 19 ላይ ለሚደረግ ምርምር የገንዘብ አስተዋጽኦ የማድረግ እንዲሁም ከወረርሽኙ ጋር በተገናኘ ትምህርት በመስተጓጎሉ ተማሪዎች የትምህርት መረጃዎችን በነጻ የሚያገኙበት ሁኔታ የማመቻቸትና የመሳሰሉ ተግባራት አከናውኗል፡፡

በበጀት ዓመቱ ኩባንያችን ከገጠሙት ተጋዳሮቶች መካከል፡ የኮቪድ- 19 በዓለም አቀፍና በሀገራችን መከሰት ኩባንያው አገልግሎቱን ለማሻሻል በሚያደርጋቸው የማስፋፊያ ሥራዎችና አገልግሎት አሰጣጥ ላይ እንዲሁም አዳዲስ ደንበኞችን ለማፍራት እንቅሰቃሴን ገድቧል፡፡ በሌላ በኩል የፋይበርና ኮፐር መስመሮች ስርቆትና መቆረጥ፣ የሃይል አቅርቦት መቆራረጥ፣ የቴሌኮም ማጭበርበር፣ የጸጥታ ችግሮችና የቴሌኮም ጣቢያዎች መትከያ ቦታ አቅርቦት መዘግየት በዋናነት የሚጠቀሱ ተግዳሮቶች ናቸው፡፡

በአጠቃላይ የኩባንያችን የበጀት ዓመቱ አፈጻጸም እጅግ የላቀና ለበለጠ ስኬት የሚነሳሳ ሲሆን በተለይም በአሁኑ ወቅት ዓለማችንና ሀገራችንን ከገጠመው የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ አንጻር የቴሌኮም አገልግሎትን ለመስጠትና ለማስፋፋት ካለው ፈታኝ ሁኔታ አንጻር አፈጻጸሙን እጅግ አመርቂ ያደርገዋል፡፡ ይህን የላቀ ውጤት ኩባንያችን ሊያስመዘግብ የቻለው የተቋሙ አመራርና ሠራተኞች ኩባንያውን በደንበኞቹና በአጋሮቹ ተመራጭ ለማድረግ ያሳዩት ቁርጠኝነት እንዲሁም ላቀዷቸው ግቦች መሳካት ያደረጉት ርብርብ በመሆኑ እጅግ የላቀ ምስጋናና አክብሮት ይገባቸዋል፡፡

በመጨረሻም ለተመዘገበው አመርቂ አፈጻጸም ለደንበኞቻችን፣ ለሥራ አጋሮቻችን እና ለባለድርሻ አካላት ምስጋናችንን እናቀርባለን፡፡

 ሐምሌ 23 ቀን 2012

This report covers performance period from 01 July to 30 June 2020

Ethio telecom commenced the budget year with the implementation of BRIDGE, the company’s three years’ strategic plan along with the 2019/20 yearly plan to realize its aspiration to become a preferred telecom service provider among customers and partners.

Aiming to achieve its strategic goals, our company conducted vast reform activities and advancements mainly focusing on enhancing customer experience and satisfaction through ensuring operational excellence; service availability, quality and affordability; effective resource utilization and enhancing financial capacity; building reputable brand and, enhancing capacity of its leadership and staff in strategy design and execution, empowerment and timely decision making.

We have harvested a total of 47.7 Billion ETB revenue, which is 105.1% of the target and 31.4% increment from the previous budget year. This outstanding achievement is scored due to network expansion, projects targeting to enhance customer experience and satisfaction, 4G/LTE full coverage in Addis Ababa and introduction of LTE advanced service in some parts of Addis, fixed broadband services with massive tariff reduction and offering 16 new and 25 revamped local and international products and services.

147.7 Million USD foreign currency was generated from international business and scored 107% of the target; showing an increase of 50% from previous budget year. This achievement is made possible because of the new commercial and technical solutions deployed to prevent telecom fraud through establishing collaborations with our international partners in a consistent and in a manner that ensures mutual benefit. Mobile voice accounts for 49% of the total revenue while Data and Internet contributes 29%, International business shares 9%, Value Added Service accounts for 9.4% and the remaining 3.6% comes from other sources.

During this period, we have paid 11.3 Billion ETB tax and 4 Billion ETB dividend, effected 10.2 Billion ETB, an equivalent of 318.4 Million USD payment for loan – for projects implemented under Vendor-financing modality. After effecting the above major and other payments, we have begun our current budget year with a positive cash position.

During the performance period, our total subscribers reached 46.2 million which is an increase of 5.8% from previous budget year. Mobile voice subscribers reached 44.5 Million, Data and Internet users 23.8 Million, Fixed Services 980K and Fixed Broadband subscribers reached 212.2 thousand. During the budget year major and multifaceted advancement was made on fixed broadband services along with tariff slash, the subscribers showed an increase of 135% from the previous budget year. As a result, telecom density has reached 46.1%.

Currently we have 16.5K indefinite and 19.9K definite term employees. To ensure sustainable business growth, various capacity building interventions were made during the budget year. As part of capacity building, we were able to provide training for 10,665 employees. Along with other interventions, employee engagement in strategy development & execution, work environment enhancement and safe & healthy working conditions, various compensation and benefits systems, enhancement of social relations by celebrating employee day throughout the company which has positively impacted working atmosphere. We have 249 thousand partners who distribute our products and services, totally we have created job and income opportunities for over 287 thousand citizens.

At the heart of our company business is our commitment to Corporate Social Responsibility. Our CSR interventions continued to have a positive impact on society, environment, and all stakeholders. Our CSR projects focused in strengthening communities by targeting the fundamental drivers of long-term development such as education, health, agriculture, environmental protection, greening and beautification of cities. We have contributed in- kind, in service, and cash accounting a total of 1.15 Billion Birr in tackling the society’s most pressing challenges that are aligned with our CSR strategic goals.

This corporate spirit is also reflected by our staff across the country by voluntarily mobilizing more than 2.1Million ETB for various humanitarian activities. Also, their material, blood donation and in-service support has been enormous.

Facing COVID-19 Pandemic, a global pandemic that substantially impacted human life and businesses, we have adopted various interventions. Our management and staff have been working to ensure connectivity as telecom service is critical to mitigate disruptions to economic and social activities of our country as the result of the Corona pandemic.

We have also committed huge resource and attention in prevention of Covid-19, from donating One Hundred Million Birr (100 Million Birr) for the cause to the very advent of COVID-19, communication and awareness creation through the replacement of ring tone message with COVID-19 related messages and providing short codes for Federal and regional governments, providing free access to Ministry of Health and Ethiopian Public Health Institute web pages providing COVID-19 related information, and availing free access to educational materials to ensure continuity amid of the pandemic, facilitating and supporting fund raising from within and abroad, financial contribution to fund Ministry of Innovation and Technology sponsored research on COVID-19, etc.

Among the challenges we faced during the period, COVID -19, which has compromised expansion and enhancement projects implementation, customer acquisition, increasing operational costs and revenue impacts, fiber and copper cable vandalism, commercial power interruption, telecom fraud, security problems and delay in land acquisition for new sites deployment were among the main ones.

In summary, our company’s performance in the budget year is generally outstanding and motivating while, particularly, remarkable given the challenges posed by the COVID-19.

As this excellent achievement is only made possible because of the stamina and commitment of our leaders and employees to make Ethio telecom a preferred operator among customers and partners and their pledge to the goals and objectives set. The leadership and employees deserve great appreciation and gratitude.

Finally, we would like to extend our most sincere gratitude to our customers, partners, and stakeholders for such outstanding performance.                                                                        

30 July 2020

Share This Post:

Share on facebook
Share on telegram
Share on twitter
Share on linkedin

Follow Us

Recent Posts

Archives